top of page

ሐምሌ 13/2015 በምስራቅ፣በሆሮጉድሩና በቄለም ወለጋ ዞኖች የሚኖሩ የአማራ ተወላጆችን እልቂት ለመፈጸም ስራ አሁንም መቀጠሉን ነዋሪዎቹ ገለጹ።



በምስራቅ፣በሆሮጉድሩና በቄለም ወለጋ ዞኖች የሚኖሩ የአማራ ተወላጆችን ላይ ዳግም እልቂት ለመፈጸም ወደ አካባቢው ገዳይ ቡድኑን የማጋዙ ስራ አሁንም መቀጠሉን ነዋሪዎቹ ለኢትዮ 360 ገለጹ።



በከፍተኛ ሁኔታ እየገባ ያለው ገዳይ ቡድን ዋና ትኩረቱን የኪረሙ ወረዳዋ ሃሮ አዲስ አለም ላይ ቢሆንም እነ ጊዳ አያና፣ጉትና ሌሎች አካባቢዎች ከሐምሌ 5 ጀምሮ እያስወረረ ነው ብለዋል።


የዚህ ገዳይ ቡድን ወደ አካባቢው እንዲገባ የተደረገ ለሌላ ሳይሆን ራሱን ተከላክሎ በህይወት የተረፈውን የአማራ ተወላጅ መጨረስ ነው ብለዋል።


አማራ ክልል ላይ ትጥቅ አስፈታለሁ ብሎ ጦርነት የከፈተው አካል ወለጋ ላይ ደግሞ በደንብ ያሰለጠነውንና መሳሪያ ያስታጠቀውን ገዳይ ቡድን እያስወረረ ነው ሲሉ ለኢትዮ 360 ገልጸዋል።


በአካባቢው ያለው የአማራ ተወላጅ ህይወቱን ለማቆየት እንደምንም ብሎ እየታገለ ባለበት በዚህ ወቅት ደግሞ ገዳይ ቡድን ተልኮበታል ብለዋል።


የአሁኑ ስብስብ ደግሞ ከተለያየ ቡድን የተዋቀረና በደንብ ስልጠና እንዲወስድ የተደረገ መሆኑንም ሳይገልጹ አላለፉም።

Recent Posts

See All

መስከረም 17/2016 በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ።

በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ። ሰራተኞቹ እየታፈኑ ያሉት ደግሞ በውስጥ በተሰገሰጉ የሰው በላው ስርአት ሃይሎች ጥቆማ ሰጭነት መሆኑን ለኢትዮ 360...

መስከረም 17/2016 በሰሜን ሸዋ ሚዳ መርሃቤቴ ላይ ገድይ ያደረገ ህዝባዊ ሃይሉ በዞኑ የተለያዩ አካባቢዎችን ከሰው በላይ ሃይል ነጻማውጣታቸውን ገለጹ

መርጦ ለማርያምን ነጻ ያወጣው ህዝባዊ ሃይል መቅደላ አምባ አምባ ዩኒቨርስቲ ውስጥና በአካባቢው በሚገኝ ካምፕ ውስጥ መሽጎ የነበረውን ይሄንን ሃይል ማጽዳት ተችሏል ብለዋል። አሁን ላይ ከሁሉም አካባቢ የተባረረው ገዳይ...

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ብርጌድ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ። በጎንደር ዙሪያ ማክሰኝት ወረዳ የጭንጫዬ አርሶ...

Email: ethio360dgre@gmail.com

Phone: 540-277-3242

PayPal ButtonPayPal Button

© 2023 by Ethio360 Media

Connect with Us

  • rumble
  • Telegram
  • TikTok

Support Us

Advertise With Us

bottom of page