top of page

ሐምሌ 20/2015ከአማራ ክልል ለህዳሴው ግድብ ደን ምንጠራ በሚል ከተወሰዱት ወጣቶች 8ቱ ህይወታቸው ማለፉን ምንጮች ገለጹ።



ከአማራ ክልል ለህዳሴው ግድብ ደን ምንጠራ በሚል ወደ አካባቢው ከተወሰዱትና ከባድ ድብደባ እየተፈጸመባቸው ካለው ወጣቶች 8ቱ ህይወታቸው ማለፉን የኢትዮ 360 ምንጮች ገለጹ።



ኢትዮ 360 በቅርቡ በ7 የህዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ ለምንጠራ ስራ በሚል በርካታ ወጣቶች ወደ ስፍራው መወሰዳቸውን በመረጃው ማውጣቱ ይታወሳል።



እነዚህ ወጣቶች ወደ ቦታው ከሄዱም በኋላ የተሰጣቸውን ስራ ጨርሰው በኋላ ደሞዛቸው ተከፍሏቸው ወደ መጡበት እንዲመለሱ ቢጠይቁም ምላሹ ግን እስርና ድብድባ እንዲሆን መደረጉንም ኢትዮ 360 ይፋ ማድረጉ ይታወቃል።


በተለይ ወጣቶቹ ምግብና ውሃ እንዳያገኙ ማድረግ ብቻ ሳይሆን በየቀኑ የሚደርስባቸው ድብደባ ህይወታቸውንና አካላቸውን እንዲያጡ አድርጓቸዋል ብለዋል።



በእባብና በጊንጥ እየተነደፉ የሚሞቱ ወጣቶች ቁጥርም ከፍተኛ መሆኑን ሳይጠቁሙ አላለፉም።


ደሞዛቸው ቀርቶባቸው ወደ ቤተሰቦቻቸው እንዲመልሷቸው ቢጠይቁም ያንን ከማድረግ ይልቅ ድብደባንና ማሰቃየትን ስራዬ ያለው አካል ወጣቶቹን እየገደላቸው ነው ሲሉ የኢትዮ 360 ምንጮች የሚፈጸመውን ኢሰብአዊ ድርጊት አጋልጠዋል።


Recent Posts

See All

መስከረም 17/2016 በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ።

በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ። ሰራተኞቹ እየታፈኑ ያሉት ደግሞ በውስጥ በተሰገሰጉ የሰው በላው ስርአት ሃይሎች ጥቆማ ሰጭነት መሆኑን ለኢትዮ 360...

መስከረም 17/2016 በሰሜን ሸዋ ሚዳ መርሃቤቴ ላይ ገድይ ያደረገ ህዝባዊ ሃይሉ በዞኑ የተለያዩ አካባቢዎችን ከሰው በላይ ሃይል ነጻማውጣታቸውን ገለጹ

መርጦ ለማርያምን ነጻ ያወጣው ህዝባዊ ሃይል መቅደላ አምባ አምባ ዩኒቨርስቲ ውስጥና በአካባቢው በሚገኝ ካምፕ ውስጥ መሽጎ የነበረውን ይሄንን ሃይል ማጽዳት ተችሏል ብለዋል። አሁን ላይ ከሁሉም አካባቢ የተባረረው ገዳይ...

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ብርጌድ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ። በጎንደር ዙሪያ ማክሰኝት ወረዳ የጭንጫዬ አርሶ...

Email: ethio360dgre@gmail.com

Phone: 540-277-3242

PayPal ButtonPayPal Button

© 2023 by Ethio360 Media

Connect with Us

  • rumble
  • Telegram
  • TikTok

Support Us

Advertise With Us

bottom of page