top of page

ሐምሌ 25/2015 በወለጋ አካባቢ ያለ የኦሮሞ ተወላጅ ሁሉ ውድ ንብረቱንም ሸጦ ቢሆን መሳሪያ እንዲገዙ መመሪያ መውረዱን ለኢትዮ 360 ገለጹ።



በኦሮሚያ ክልል በተለይ በወለጋ አካባቢ ያለ የኦሮሞ ተወላጅ ሁሉ ውድ ንብረቱንም ሸጦ ቢሆን መሳሪያ እንዲገዛ አዲስ መመሪያ መውረዱን በአካባቢው የሚኖሩ የአማራ ተወላጆች ለኢትዮ 360 ገለጹ።



የሰው በላው ስርአት የወረደው መመሪያ በተለይ በምስራቅ ወለጋ፣በሆሮጉድሩና በአካባቢው ያሉ የኦሮሞ ተወላጆች ሁሉ መሳሪያ እንዲገዙ አዲስ መመሪያ ወርዷል ብለዋል።



አማራው ራሱ በገዛው መሳሪያ ነው ራሱን እየተከላከለ ያለው ስለዚህ እሱንም ማስለቀቅ ያልቻላችሁት ለዛ ነው በሚል ቅስቀሳ እየተደረገላቸው መሆኑን ያነሳሉ።


እነሱ መሳሪያውን ከገዙ በኋላ ደግሞ ስልጠናውም ሆነ ግብአቱ ከዚሁ የገዳዮች ስብስብ እንደሚሟላለት ቃል ተገብቶለታል ብለዋል።



ከሐምሌ 21 ጀምሮም ስልጠና መሰጠት መጀመሩንም ሳይጠቁሙ አላለፉም።


ከሳምንት ወይንም ከሁለት ሳምንት በኋላ አማራውን መጨፍጨፍ ይጀመራል የሚሉት የአማራ ተወላጆቹ ያለው እንቅስቃሴ ከበፊቱ ለየት ያለ በመሆኑ አስፈሪ ነው ሲሉ ገልጸውታል።



ሊፈጸም የታሰበውን የዘር ማጥፋት ወንጀል ሁሉም ወለጋ ካለው የአማራ ተወላጅ ጎን በመቆም እንዲያስቆምለት ጥሪያቸውን አቅርበዋል።



Recent Posts

See All

መስከረም 17/2016 በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ።

በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ። ሰራተኞቹ እየታፈኑ ያሉት ደግሞ በውስጥ በተሰገሰጉ የሰው በላው ስርአት ሃይሎች ጥቆማ ሰጭነት መሆኑን ለኢትዮ 360...

መስከረም 17/2016 በሰሜን ሸዋ ሚዳ መርሃቤቴ ላይ ገድይ ያደረገ ህዝባዊ ሃይሉ በዞኑ የተለያዩ አካባቢዎችን ከሰው በላይ ሃይል ነጻማውጣታቸውን ገለጹ

መርጦ ለማርያምን ነጻ ያወጣው ህዝባዊ ሃይል መቅደላ አምባ አምባ ዩኒቨርስቲ ውስጥና በአካባቢው በሚገኝ ካምፕ ውስጥ መሽጎ የነበረውን ይሄንን ሃይል ማጽዳት ተችሏል ብለዋል። አሁን ላይ ከሁሉም አካባቢ የተባረረው ገዳይ...

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ብርጌድ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ። በጎንደር ዙሪያ ማክሰኝት ወረዳ የጭንጫዬ አርሶ...

bottom of page