top of page

ሐምሌ 6/2015በአዲስ አበባ ቤተመንግስት ዙሪያ በጥበቃ ስራ ተሰማርተው የነበሩ ከ250 በላይ የአማራ ተወላጆች ትጥቅ እንዲፈቱ ተደርገጉ ።



በአዲስ አበባ ቤተመንግስት ዙሪያ በጥበቃ ስራ ተሰማርተው የነበሩ ከ250 በላይ የአማራ ተወላጆች ትጥቅ እንዲፈቱ ተደርገው በብላቴ ወታደራዊ ማሰልጠኛ መታሰራቸውን የኢትዮ 360 ምንጮች ገለጹ።


እነዚህ የአማራ ተወላጅ የሆኑ የሰራዊቱ አባላት ለረጅም አመታት በታማኝነት ቤተመንግስቱንና አካባቢውን ሲጠብቁ የኖሩ መሆናቸውን ይናገራሉ።


ነገር ግን ሰው በላው ስርአት መምጣቱን ተከትሎ ግን ውስጥ ለውስጥ ከፍተኛ የሆነ መገለል ሲፈጸምባቸው መቆየቱን ይናገራሉ።


ይሄንን ሁሉ መገለልና የተለያዩ ጫናዎች ሲያደርስባቸው የቆየው አካል አሁን ደግሞ መሳሪያቸውን ነጥቆ ወደ ብላቴ ማሰልጠኛ ማእከል እንዲወሰዱ አድርጎ አፍኗቸዋል ብለዋል::


እንደ ምንጮቹ ከሆኑ ከ250 በላይ የሚሆኑት የአማራ ተወላጆች ወደ ብላቴ ተወስደው መታሰራቸውን እንጂ ወደዛ ከተወሰዱ በኋላ ግን ስለተፈጸመባቸው ሰብአዊ ጥሰት የታወቀ ነገር የለም ይላሉ።


አሰበ ተፈሪ ላይ መሳሪያቸውን አስቀምጠው ስፖርት ሲሰሩ ከነበሩት የመከላከያ አባላት መካከል በብሄራቸው ተመርጠው የተገደሉት የአማራ ተወላጆችን ጨምሮ በየአካባቢው የሚገደሉ የአማራ ተወላጅ የሰራዊቱ አባላት ቁጥር ከፍተኛ መሆኑንም ሳይጠቁሙ አላለፉም።


በቅርቡ ወለጋ ላይ በዛው ተወልደው ያደጉና የሰራዊቱ አባላት የነበሩ የአማራ ተወላጆችም በአደባባይ ተመርጠው መገደላቸውን ኢትዮ 360 በመረጃው ማውጣቱ ይታወሳል።


Recent Posts

See All

መስከረም 17/2016 በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ።

በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ። ሰራተኞቹ እየታፈኑ ያሉት ደግሞ በውስጥ በተሰገሰጉ የሰው በላው ስርአት ሃይሎች ጥቆማ ሰጭነት መሆኑን ለኢትዮ 360...

መስከረም 17/2016 በሰሜን ሸዋ ሚዳ መርሃቤቴ ላይ ገድይ ያደረገ ህዝባዊ ሃይሉ በዞኑ የተለያዩ አካባቢዎችን ከሰው በላይ ሃይል ነጻማውጣታቸውን ገለጹ

መርጦ ለማርያምን ነጻ ያወጣው ህዝባዊ ሃይል መቅደላ አምባ አምባ ዩኒቨርስቲ ውስጥና በአካባቢው በሚገኝ ካምፕ ውስጥ መሽጎ የነበረውን ይሄንን ሃይል ማጽዳት ተችሏል ብለዋል። አሁን ላይ ከሁሉም አካባቢ የተባረረው ገዳይ...

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ብርጌድ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ። በጎንደር ዙሪያ ማክሰኝት ወረዳ የጭንጫዬ አርሶ...

Email: ethio360dgre@gmail.com

Phone: 540-277-3242

PayPal ButtonPayPal Button

© 2023 by Ethio360 Media

Connect with Us

  • rumble
  • Telegram
  • TikTok

Support Us

Advertise With Us

bottom of page