top of page

መስከረም 10/2015 በጎጃም ደብረማርቆስ ያለውን የገዳዩን ቡድን ምሽግ የተቆጣጠረው አባዛኛውን አካባቢዎ ነጻ እያወጣ መሆኑን የህዝባዊ ሃይሉ አባላት ገለጹ።



በጎጃም ደብረማርቆስ ያለውን የገዳዩን ቡድን ምሽግ የተቆጣጠረው ህዝባዊ ሃይሉ አባዛኛውን አካባቢዎ ነጻ እያወጣ መሆኑን የህዝባዊ ሃይሉ አባላት ለኢትዮ 360 ገለጹ።


ዛሬ መርጦ ለማርያምና ሞጣ ላይ ህዝባዊ ሃይሉ ውጊያ ላይ ነው የሚሉት የህዝባዊ ሃይሉ አባላት ማርቆስ ላይም በተወሰነ ደረጃ ውጊያ መኖሩን ይናገራሉ።


አካባቢውን ለቆ የወጣው ገዳይ ቡድን ግን ወደ ሽምቅ ውጊያ ገብቷል ሲሉ ያለውን እውነታ ይናገራሉ።


ገዳይ ቡድኑ የአማራ ህዝባዊ ሃይልን በምንም መልኩ ማሸነፍ እንደማይችል ማወቁን ተከትሎ ውጊያውን ወደ ሽምቅ ሊያዞር መሆኑን ኢትዮ 360 አስቀድሞ በመረጃው ይፋ ማድረጉ ይታወሳል።

ቡሬና ፍኖተ ሰላምን ነጻ ያደረገው ህዝባዊ ሃይሉ አማኑኤልንም ሙሉ በሙሉ ነጻ አድርጎና የገዳዩን ቡድን ምሽግ ሰብሮ አካባቢውን ተቆጣጥሯል ብለዋል።


ኢንተርኔት አቋረጦ ህዝባዊ ሃይሉን አመታለሁ ብሎ ያሰበው ገዳይ ቡድን ትልቅ ነው የሚባለውንና መሽጎበት የነበረውን የኮሶበር ማዘዣ ጣቢያውንም በራሱ ጊዜ ለቆ እንዲሄድ ሆኗል ትላንት ምሽትም ህዝባዊ ሃይሉ ተቆጣጥሮታል ብለዋል።


ከባህርዳር ተነስቶ መራዊ እገባለሁ ብሎ ያሰበው ሃይልም መራዊ ላይ እንዲመለስ ሆኗል የሚሉት የህዝባዊ ሃይሉ አባላት ከደንበጫና ከደብረማርቆስ ውጪ ሌላው አካባቢ ነጻ ነው ሲሉ ይናገራሉ።

ደጀን፣ሞጣና ባህርዳር ላይ ያለው ሁኔታም ቢሆን ብቸና ላይ በተወሰነ ደረጃ የሚንቀሳቀሰው ገዳይ ቡድን በሽምቅ ህዝባዊ ሃይሉን ለመውጋት እየሞከረ ነው ሲሉ ለኢትዮ 360 ገልጸዋል።

Recent Posts

See All

መስከረም 17/2016 በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ።

በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ። ሰራተኞቹ እየታፈኑ ያሉት ደግሞ በውስጥ በተሰገሰጉ የሰው በላው ስርአት ሃይሎች ጥቆማ ሰጭነት መሆኑን ለኢትዮ 360...

መስከረም 17/2016 በሰሜን ሸዋ ሚዳ መርሃቤቴ ላይ ገድይ ያደረገ ህዝባዊ ሃይሉ በዞኑ የተለያዩ አካባቢዎችን ከሰው በላይ ሃይል ነጻማውጣታቸውን ገለጹ

መርጦ ለማርያምን ነጻ ያወጣው ህዝባዊ ሃይል መቅደላ አምባ አምባ ዩኒቨርስቲ ውስጥና በአካባቢው በሚገኝ ካምፕ ውስጥ መሽጎ የነበረውን ይሄንን ሃይል ማጽዳት ተችሏል ብለዋል። አሁን ላይ ከሁሉም አካባቢ የተባረረው ገዳይ...

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ብርጌድ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ። በጎንደር ዙሪያ ማክሰኝት ወረዳ የጭንጫዬ አርሶ...

bottom of page