top of page

መስከረም 10/2016 በሰሜን ሸዋ ራሳ ላይ ጦርነት የከፈተው ገዳይ ቡድን አብዛኞቹን አካባቢዎች እንዲለቅ መደረጉን አባላቱ ገለጹ


ከከሚሴ የገባው ገዳይ ቡድን ጭራ ሜዳ ላይ ከነሙሉ ሰራዊቱ ከጥቅም ውጪ እንዲሆን መደረጉን ይናገራሉ።


ሰላ ድንጋይን ነጻ ያወጣው ሃዝባዊ ሃይልን እየሸሸው ያለው ገዳይ ቡድኑ ብቻ ሳይሆን ሆድ አደሩ የብአዴን ቡድን መሆኑ ነው የሚናገሩት።


የተከበበው ሃይሉን ለማስለቀቅ የገባው ገዳይ ቡድን ጣርማ በር ላይ ከባድ ውጥረት ላይ ገብቷል ብለዋል።


አንኮበር ላይ የተኩስ ልውውጥ እንደነበር የሚናገሩት የህዝባዊ ሃይሉ አባላት በዚህ ጦርነት ደግሞ የአፋር ሃይል ከአማራ ወገኑ ጎን ተሰልፎ እንደነበርም ገልጸዋል።


በአካባቢው የወደቀውን አስከሬኑን መሰብሰብ ያልቻለው ገዳይ ቡድን ወደ ከተማ ለመግባት ቢሞክርም መረጋጋት ግን አልቻለም ብለዋል።


ዘርቃሚ ላይም ጦርነት የከፈተው ገዳይ ቡን በሚገባው መልኩ ዋጋውን አግኝቷል ሲሉ ለኢትዮ 360 ገልጸዋል።

ከበባው ውስጥ የገባው ገዳይ ቡድን ያፈናቸውን የከተማዋን አንቂዎች፣የሃይማኖት አባቶችና ሌሎችን ወደ ሌላ አካባቢው ለመውሰድ ያደረገ ጥረትም በህብረተሰቡ ትግል ሊሳካለት አልቻለም ሲሉ ገልጸዋል።

ወደ ድምድምና በቆላማው አካባቢ የነበርው ገዳይ ቡድን በቆረጣ ተከታታይ ጥቃት እንደተፈጸመበትም ይናገራሉ።


ይሄንን ሽንፈት መቀበል ያልቻለው ገዳይ ቡድን ከባድ መሳሪያውን ወደ አገኘው አቅጣጫ እየተኮሰ መሆኑንም ሳይጠቁሙ አላለፉም።


የወንጭት ተፋሰስን ይዘው የመጡ የዚሁ ሃይል አባላት ደግሞ ህዝባዊ ሃይሉን መቀላቀላቸውን ነው የሚናገሩት

መንዲዳ ላይ ምንም አይነት እንቅስቃሴ እንዳይኖር አድርጎ የቆየው ገዳይ ቡድን ነቅሎ ወደ አዲስ አበባ እየሸሸ መሆኑን ነው የሚናገሩት።

ህዝባዊ ሃይሉ በዚህ መልኩ ትግል ሲያደርግ የሆድ አደሩ ስብስብ ደግሞ ንጹሃንን በማሳሰርና በመጠቆም ስራ ላይ ተሰማርቷል ብለዋል።


እነዚህ ደግሞ በቃችሁ ሊባሉ ይገባል ሲሉም ለኢትዮ 360 ገልጸዋል።



Recent Posts

See All

መስከረም 17/2016 በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ።

በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ። ሰራተኞቹ እየታፈኑ ያሉት ደግሞ በውስጥ በተሰገሰጉ የሰው በላው ስርአት ሃይሎች ጥቆማ ሰጭነት መሆኑን ለኢትዮ 360...

መስከረም 17/2016 በሰሜን ሸዋ ሚዳ መርሃቤቴ ላይ ገድይ ያደረገ ህዝባዊ ሃይሉ በዞኑ የተለያዩ አካባቢዎችን ከሰው በላይ ሃይል ነጻማውጣታቸውን ገለጹ

መርጦ ለማርያምን ነጻ ያወጣው ህዝባዊ ሃይል መቅደላ አምባ አምባ ዩኒቨርስቲ ውስጥና በአካባቢው በሚገኝ ካምፕ ውስጥ መሽጎ የነበረውን ይሄንን ሃይል ማጽዳት ተችሏል ብለዋል። አሁን ላይ ከሁሉም አካባቢ የተባረረው ገዳይ...

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ብርጌድ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ። በጎንደር ዙሪያ ማክሰኝት ወረዳ የጭንጫዬ አርሶ...

bottom of page