መስከረም 3/2015 በደብረታቦር እስር ቤት እየተንገላቱ የሚገኙት የአማራ ልዩ ሃይል እንዳይወጡ መከልከሉን የኢትዮ 360 ምንጮች ገለጹ።
- Ethio 360 Media 2
- Sep 14, 2023
- 1 min read
በደብረታቦር እስር ቤት እየተንገላቱ የሚገኙት የአማራ ልዩ ሃይል አሰልጣኞች ፍርድ ቤት ነጻ እንዲወጡ ትእዛዝ ቢሰጥም የፖሊስ መምሪያው ግን እንዳይወጡ መከልከሉን የኢትዮ 360 ምንጮች ገለጹ።
በነሃሴ 29/2015 ነጻ ተብለው የተሳነበቱት የልዩ ሃይል አሰልጣኞች በፖሊስ መመሪያው ሃላፊ ኮሚሽነር አየልኝ ትእዛዝ ሰጭነት እንይፈቱ መደረጉን ተናግረዋል።
ነገር ግን ታራሚዎቹ ለምን አንፈታም በሚል ላቀረቡት ጥያቄ ኮማንድ ፖስቱ ነው እንዳትፈቱ ያዘዘው የሚል ምላሽ እንደተሰጣቸውም ይናገራሉ።
ስለጉዳዩ የተጠየቀው ኮማንድ ፖስት ግን በዚህኛው ኮማንድ ፖስት ጊዜ የታሰሩ ስላልሆኑ እኛ አንፈልጋቸውም በሚል ቁርጥ ያለ ምላሽ መስጠቱንም አስታውቀዋል።
ይሄንን ሁሉ ምክንያት እየፈጠሩና እነዚህ ወጣቶች እንዳይፈቱ እያደረጉ ያሉት የብአዴን ሆድ አደር ስብስቦች አሰልጣኞቹ ቢፈቱ ለህዝባዊ ትግሉ ትልቅ ድጋፍ ያደርጋሉ የሚል ስጋት ስላደርባቸው ብቻ ነው ሲሉ ሁኔታውን አስቀምጠዋል።
አሁን ላይ ወጣቶቹ እየተንገላቱና በእስር እየማቀቁ ያሉት ምንም ጥፋት ኖሮባቸው ሳይሆን የግለሰቦች የግል እስረኛ በመሆናቸ ነው ሲሉ የኢትዮ 360 ምንጮች ገልጸዋል።