top of page

ሰኔ 22/2015የብአዴን ሁሉም አመራሮችና መገናኛ ብዙሃኑ ስለልማትና መሰል ጉዳዮች ብቻ እንዲያወሩ መመሪያ ወርደ


አሁን ላይ ሁሉም የብአዴን ሹመኞች እና ሚዲያወቻቸው ስለልምትና መሰል ጉዳዮችን ብቻ እንዲናገሩ፥ እንዲጽፉ በመወረደላቸው መመሪያ መሰረት ተግባራዊ እያደረጉት ነው ይላሉ።



እንደማሳያም ሰሞኑን የክልሉ ቴሌቪዥን ጣቢያና የባሃርዳር ከንቲባን ጨምሮ አብዛኛውም አመራር የሚለጥፈው የልማት ጉዳይ ብቻ ነው በሚል ያቀርባሉ።



ይሄንን ማድረግ ያስፈለገው ደግሞ አሁን ላይ ሁሉም አይኑንና ብእሩን ኦህዴድ በአማራ ክልልና ህዝብ ላይ እየፈጸመ ባለው ወንጀል ላይ በማድረጉ ነው ይላሉ።



እናም ይሄን አጀንዳ ለመቀልበስና የህዝቡን ልብ ለመክፈል አመራሩም ሆነ መገናኛ ብዙሃኖቻቸው ትኩረታቸውን በልማትና መሰል ጉዳዮች ላይ እንዲያደርጉ ቤተመንግስቱን ከተቆጣጠረው ግለሰብ ትእዛዝ መሰጠቱን ገልጸዋል።



አሁን ላይ የብአዴኑ ጥቅመኛ ስብስብ ህዝባዊ ትግሉን ለመጎተትና አማራውን ለማስበላት ያለውን አቅም ሁሉ እየተጠቀመ መሆኑን ሳይጠቁሙ አላለፉም።



በተለይ ደግሞ ከላይ ካለው ጀምሮ እስከ ታችኛው እርከን ያለው የብአዴን ስብስብ በጥቅም የተሳሰረ መሆኑ ደግሞ ነገሩን አክፍቶታል ሲሉ ምንጮቹ ገልጸዋል።


Recent Posts

See All

መስከረም 17/2016 በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ።

በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ። ሰራተኞቹ እየታፈኑ ያሉት ደግሞ በውስጥ በተሰገሰጉ የሰው በላው ስርአት ሃይሎች ጥቆማ ሰጭነት መሆኑን ለኢትዮ 360...

መስከረም 17/2016 በሰሜን ሸዋ ሚዳ መርሃቤቴ ላይ ገድይ ያደረገ ህዝባዊ ሃይሉ በዞኑ የተለያዩ አካባቢዎችን ከሰው በላይ ሃይል ነጻማውጣታቸውን ገለጹ

መርጦ ለማርያምን ነጻ ያወጣው ህዝባዊ ሃይል መቅደላ አምባ አምባ ዩኒቨርስቲ ውስጥና በአካባቢው በሚገኝ ካምፕ ውስጥ መሽጎ የነበረውን ይሄንን ሃይል ማጽዳት ተችሏል ብለዋል። አሁን ላይ ከሁሉም አካባቢ የተባረረው ገዳይ...

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ብርጌድ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ። በጎንደር ዙሪያ ማክሰኝት ወረዳ የጭንጫዬ አርሶ...

bottom of page