top of page

በአዲስ አበባ ተጽእኖ ፈጣሪ ናቸው የሚባሉ መምህራን ሊታፈኑ ነው።(ኢትዮ 360-ሚያዚያ 25/2015)


(ኢትዮ 360-ሚያዚያ 25/2015)በአዲስ አበባ ከተማ ተጽእኖ ፈጣሪ ናቸው የሚባሉ የአማራ ተወላጅ መምህራንን ለማፈን አዲስ መመሪያ መውረዱን የኢትዮ 360 ምንጮች ገለጹ።


ሰሞኑን ከየቦታው የእጅ ስልካቸው ጭምር እየተቀማ ወደ አልታወቀ ስፍራ የተወሰዱ መምህራንና በከተማዋ በተለያዩ መስኮች የተሰማሩ የአማራ ተወላጆች መኖራቸውን ያነሳሉ።


ሰሞኑ ታፍነው ከተወሰዱት መካከል ከባድ ድብደባና ማንገላታት ተፈጽሞባቸው ከታፈኑበት የተለቀቁት ደግሞ ወደ ቤታቸው ሲመለሱ ቤታቸው ለባለጊዜዎች ተሰቶ የእነሱ ንብረትና ልጆቻቸውን አደባባይ ተጥለው ማግኘታቸውንም ሳይጠቁሙ አላለፉም።


በየቀበሌው የሚሰሩና በቢሮ ደረጃ ያሉ ሀላፊዎች የአማራ ተወላጆች በመሆናቸው ብቻ የእጅ ስላካቸውን ተነጥቀው ወዳልታወቀ ስፍራ እየተደበደቡ ከተወሰዱ በኋላ እስካሁን የትእንደደረሱ አለመታወቁንም ያነሳሉ።


በተለይ በአማራ ክልል ህዝብ ላይ የዘር ማጥፋት ዘመቻ ከታወጀ በኋላ በአዲስ አበባ ከተማ የሚካሄደው አይን ያወጣ አፈና ተጠናክሮ ቀጥሏል ሲሉ ምንቾቹ ተናግረዋል።


በትንሹ ይላሉ አንድ ሳምንት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ከ20ሺ በላይ የሚሆኑ የአማራ ተወላጆች በዚሁ ጨካኝ ስርአት መታፈናቸውን ነው የተናገሩት።


በዚህ እስር ውስጥ ደግሞ ከአማራው ጋር ወግናችኋል የተለየ ቅርርብ አላችሁ በሚል ብቻ አብረው የታፈኑ የአዲስ አበባና የደቡብ ክልል ተወላጅ ወጣቶች እንደሚገኙበትም ነው ያስቀመጡት።


ከየአካባቢው የሚታፈንውን ወጣት ለማጎር ደግሞ በከተማዋ የግለሰብ ቤቶች ሁሉ ሳይቀሩ ወደ እስር ቤትነት ተቀይረዋል ብለዋል።


በተለይ በከተማ በቀ ስራ የተሰማሩ ወጣቶች፣ሊስትሮዎች፣ቡና በማፍላት የሚተዳደሩ ሴቶችና ሌሎችም የዚሁ አፋኝ ቡድን ሰለባ መሆናቸውን ያስቀምጣሉ።


ሰሞኑን ይላሉ አያት አደባባይ አካባቢ ለአካል ጉዳተኞች የስራ ፈጠራ በሚል የሰጧቸውን ቦታ ከነንብረቱ ያፈራረሰው አካል ሁለት አካል ጉዳተኞችንም አፍኖ መውሰዱን ነው የኢትዮ 360 ምንጮች የተናገሩት።


በዚሁ ቡድን የሚታፈነው ወጣት በሚያርፍበት ቦታ የሚሰጠው ነገር ቢኖር በቀን አንዲት ኮቾሮ ሲሆን ውሃም ሆነ ወደ ውጪ ወቶ አየር እንዲያገኝ የሚደረግበት ምንም አይነት አጋጣሚ አለመኖሩንም ነው ከእስር የተፈቱት የአማራ ተወላጆች የሚናገሩት።


በሺዎች የሚቆጠሩ የአማራ፣የአዲስ አበባና የደቡብ ክልል ወጣቶችን ያሰረው አካል ዛሬም አፈናውን ቀጥሏል ሲሉ የአይን እማኞች ለኢትዮ 360 ገልጸዋል።


Recent Posts

See All

መስከረም 17/2016 በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ።

በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ። ሰራተኞቹ እየታፈኑ ያሉት ደግሞ በውስጥ በተሰገሰጉ የሰው በላው ስርአት ሃይሎች ጥቆማ ሰጭነት መሆኑን ለኢትዮ 360...

መስከረም 17/2016 በሰሜን ሸዋ ሚዳ መርሃቤቴ ላይ ገድይ ያደረገ ህዝባዊ ሃይሉ በዞኑ የተለያዩ አካባቢዎችን ከሰው በላይ ሃይል ነጻማውጣታቸውን ገለጹ

መርጦ ለማርያምን ነጻ ያወጣው ህዝባዊ ሃይል መቅደላ አምባ አምባ ዩኒቨርስቲ ውስጥና በአካባቢው በሚገኝ ካምፕ ውስጥ መሽጎ የነበረውን ይሄንን ሃይል ማጽዳት ተችሏል ብለዋል። አሁን ላይ ከሁሉም አካባቢ የተባረረው ገዳይ...

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ብርጌድ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ። በጎንደር ዙሪያ ማክሰኝት ወረዳ የጭንጫዬ አርሶ...

Email: ethio360dgre@gmail.com

Phone: 540-277-3242

PayPal ButtonPayPal Button

© 2023 by Ethio360 Media

Connect with Us

  • rumble
  • Telegram
  • TikTok

Support Us

Advertise With Us

bottom of page