top of page

ነሐሴ 11/2015 በባህርዳር ከተማ በስድስቱም ክፍለ ከተሞች ባሉ የብልጽግናው ጽህፈት ቤቶች ላይ ትላንት ምሽት ጥቃት መፈጸመኑን አስታወቁ።

ነሐሴ 11/2015

በባህርዳር ከተማ በስድስቱም ክፍለ ከተሞች ባሉ የብልጽግናው ጽህፈት ቤቶች ላይ ትላንት ምሽት ጥቃት መፈጸመኑን የኢትዮ 360 ምንጮች አስታወቁ።


ምሽት አንድ ሰአት ላይ በስድስቱም ጽህፈት ቤቶች ላይ ከተፈጸመው ጥቃት ጋር ተያይዞ ምን ይህል ጉዳት እንደደረሰ እስካሁን አለመታወቁንም አመልክተዋል።


በስድስቱም ጽህፈት ቤቶች በተመሳሳይ ሰአት የተፈጸመው ጥቃት የተወሰደው ደግሞ ባልታወቁ ሰዎች መሆኑንም ምንጮቹ አንስተዋል።


ይህ በእንዲህ እንዳለ ደግሞ በባህርዳና ዙሪያው የሚቀሳቀሰው ህዝባዊ ሃይሉ በተደጋጋሚ በገዳዩ ቡድንም ሆነ በሆድ አደሩ የብአዴን ሚሊሻና አድማ ብተና ላይ ከፍተኛ ቁጠ ያለው መሳሪያን መማረኩን ይናገራሉ።


በቅርቡ ሁለት ፓትሮል የአድማ ብተና ሃይል ጥቃት ሊፈጽም ወደነሱ ቢላክም እነሱ ግን ይዞት የመጣውን 36 መሳሪያና አንድ መትረየስ ከነሃይሉ መማረኩንም ይናገራሉ።


ከዛም ሌላ ከ100 በላይ ክላሾችን በቀላሉ የማረከው ይሄው የህዝባዊ ሃይሉ ቡድን የማረካቸውን የአድማ ብተና አባላት ስልጠና ሰተው በሰላም ወደ ቤተሰቦቻቸው እንዲመለሱ ማድረጉንም አመልክተዋል።


ከፌደራል የመጣው ጢስ አባይ ላይ ሊገላቸው የመጣውን የገዳዩን ስርአት ሙሉ በሙሉ ሲደመስስ 18ቱ ደግሞ በገዛ ፈቃዳቸው እጃቸውን እንደሰጡ ይናገራሉ።


የክልሉ ኮሚሽነር ደስዬ ደጀን ቀኝ እጅ የሚባለውን ዋና ኢንስፔክተር ሙቀት የሚባለውን የማረከው ህዝባዊ ሃይል የ10ኛ ፖሊስ ጣቢያን ተቆጣጥሬያለሁ ብሎ ያስብ የነበረው ሃይልም ወገኔን አልወጋም በሚል ከነሱ ጋር እንዲቀላቀል ማድረጉን ነው የኢትዮ 360 ምንጮች የሚናገሩት።


አሁንም ከተማ ላይ በገዳዩ ስርአት በንጹሃን ላይ የተጀመረውን ግድያ ለማስቆም ከከተማው ይራቅ እንጂ ተልእኮውን ግን በአግባቡ እየፈጸመ ነው ሲሉ ምንጮቹ አመልክተዋል።

Recent Posts

See All

መስከረም 17/2016 በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ።

በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ። ሰራተኞቹ እየታፈኑ ያሉት ደግሞ በውስጥ በተሰገሰጉ የሰው በላው ስርአት ሃይሎች ጥቆማ ሰጭነት መሆኑን ለኢትዮ 360...

መስከረም 17/2016 በሰሜን ሸዋ ሚዳ መርሃቤቴ ላይ ገድይ ያደረገ ህዝባዊ ሃይሉ በዞኑ የተለያዩ አካባቢዎችን ከሰው በላይ ሃይል ነጻማውጣታቸውን ገለጹ

መርጦ ለማርያምን ነጻ ያወጣው ህዝባዊ ሃይል መቅደላ አምባ አምባ ዩኒቨርስቲ ውስጥና በአካባቢው በሚገኝ ካምፕ ውስጥ መሽጎ የነበረውን ይሄንን ሃይል ማጽዳት ተችሏል ብለዋል። አሁን ላይ ከሁሉም አካባቢ የተባረረው ገዳይ...

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ብርጌድ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ። በጎንደር ዙሪያ ማክሰኝት ወረዳ የጭንጫዬ አርሶ...

bottom of page