top of page

ነሐሴ 2/2015 የባህርዳር ከተማ ለሊቱን ሙሉ በከባድ መሳሪያ ሲደብደብ ማደሩን ነዋሪዎቹ ገለጹ።



የባህርዳር ከተማ ለሊቱን ሙሉ በከባድ መሳሪያ ሲደብደብ ማደሩን ነዋሪዎቹ ለኢትዮ 360 ገለጹ።


የአማራ ህዝባዊ ሃይሉ ደግሞ የሳባታሚት ማረሚያ ቤትን ሰብሮ በሺዎች የሚቆጠሩ የፋኖ፣የልዩ ሃይል፣የጦር መኮንኖችንና ሌሎችን ነጻ ማውጣታቸውንም ይናገራሉ።


ይሄን እያደረጉ ባለበት ሰአት ደግሞ መኮድና ቀበሌ 14 አካባቢ ከባድ የሆነ የከባድ መሳሪያ ተኩስ እንደነበርም ተናግረዋል።

ቤተክርስቲያን የሚሄድ ምእመናን ሳይቀር በዚሁ ገዳይ ቡድን እየተመቱ ነው የሚሉት ነዋሪዎቹ እየተደረገ ያለው ነገር ከተማዋን የማውደም ስራ ነው ሲሉም ገልጸዋል።


በአማራ ህዝብ ላይ የዘር ማጥፋት ጭፍጨፋ እየተፈጸመ መሆኑንም ሁሉም እንዲያቀው መደረግ አለበት ባይ ናቸው።


ሞርተርና ታንክን ጨምሮ ሌሎች ከባድ መሳሪያዎችም ወደ ህዝቡና ወደ ከተማው በመወንጨፍ ላይ ናቸው ሲሉም ነዋሪዎቹ ገልጸዋል።

የብአዴኑ አመራር ከተማዋን አስቀድሞ ዘርፎ ነው የሄደው የሚሉት ነዋሪዎቹ ወደ ክልሉ የገባው ሃይል ደግሞ አካባቢውን እያወደመ ነው ሲሉ ገልጸውታል።


ሁሉም አማራ ነኝ የሚል በመላው አላም የሚኖር በሙሉ በዚህ ትግል ውስጥ ጩህቱን ሊያሰማ ይገባል ሲሉ ነዋሪዎቹ ለኢትዮ 360 ገልጸዋል።


ባህርዳር በቀበሌ14፣ ድባጤ፣ ገጠርመንገድ ብዙሐን መገናኛና በመኮድ አካባቢ ህዝባዊ ሃይሉ መብረቃዊ የሆነ ጥቃት በገዳዩ ብዱን ላይ ማድረሱንም ሳይጠቁሙ አላለፉም።


ከለሊቱ 9 ሰዓት ጀምሮም ከባድ ውጊያ እያካሄደ ነው የሚሉት ምንጮቹ በዚህ ደግሞ የሰሜን ምዕራብ ዕዝ እንዲዳከም አድርጎታል ብለዋል።


በዚህ የተዳከመው ስብስብ የኮማንዶ ሃይልን አምጥቶ በውጊያው ከመጠቀሙም በላይ ከባድ መሳሪያዎችን በንጹሃን ቤት ላይ ሲተኩስ ማደሩንም ሳይጠቁሙ አላለፉም።


Recent Posts

See All

መስከረም 17/2016 በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ።

በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ። ሰራተኞቹ እየታፈኑ ያሉት ደግሞ በውስጥ በተሰገሰጉ የሰው በላው ስርአት ሃይሎች ጥቆማ ሰጭነት መሆኑን ለኢትዮ 360...

መስከረም 17/2016 በሰሜን ሸዋ ሚዳ መርሃቤቴ ላይ ገድይ ያደረገ ህዝባዊ ሃይሉ በዞኑ የተለያዩ አካባቢዎችን ከሰው በላይ ሃይል ነጻማውጣታቸውን ገለጹ

መርጦ ለማርያምን ነጻ ያወጣው ህዝባዊ ሃይል መቅደላ አምባ አምባ ዩኒቨርስቲ ውስጥና በአካባቢው በሚገኝ ካምፕ ውስጥ መሽጎ የነበረውን ይሄንን ሃይል ማጽዳት ተችሏል ብለዋል። አሁን ላይ ከሁሉም አካባቢ የተባረረው ገዳይ...

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ብርጌድ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ። በጎንደር ዙሪያ ማክሰኝት ወረዳ የጭንጫዬ አርሶ...

bottom of page