top of page

ኢትዮ 360 - ሐምሌ 19/2015)በዱባይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ፓስፖርት የሚያድስላቸው አካል ጠፍቶ ለከፋ ችግር ተጋልጠዋል።


በተባበሩት አረብ ኢምሬትስ ዱባይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ፓስፖርት የሚያድስላቸው አካል በማጣታቸው ለከፋ ችግር መጋለጣቸውን ለኢትዮ 360 ገለጹ።


ፓስፖርት ለማሳደስ ኤምባሲውን ሲለምኑ ወደ ሰባት ወራትን ማስቆጠሩን ይናገራሉ።

ከኤምባሲው ጠብቁ የሚሉ ተደጋጋሚ ምላሾች ቢሰጡም እስካሁን ግን በመጠበቅ የተገኘ ነገር የለም ብለዋል።


እስከ ሰኔ 30 ፓስፖርታችሁ ታድሶ ይመጣሉ የሚል ቃል ተገብቶ የነበረ ቢሆንም እስካሁን ግን ምንም ሊያደርጉ አልቻሉም ብለዋል።


ፓስፖርታቸውን ለማሳደስ ለኤምባሲው በሰጡበት እዛው የመገልገያ ጊዜውን እንደተቃጠለም ሳይገልጹ አላለፉም።


ነጭ ወረቀት ሰቶ በእሱ ተጠቀሙ የሚለው ኤምባሲ በራሱ መፍትሄ ለማምጣት አልቻለም ብለዋል።

አምባሳደሩን ጭምር አናግረናል የሚሉት ኢትዮጵያውያኑ ነገር ግን ማንም የመፍትሄው አካል ሊሆን ባለመቻሉ ኢትዮጵያውያኑ በአሰሪዎቻቸው ያለምንም ማስረጃ እየተጫኑ መሆኑን አስታውቀዋል።


በሰው ሃገር ያለፓስፖርት መንቀሳቀስም ሆነ የቤት ኪራይ መክፈልም ሆነ የባንክ አገልግሎት ማግኘት እንደማይቻል እየታወቀ ማንም ግን ሊያግዛቸው እንዳልቻለ ነው ለኢትዮ 360 የገለጹት።


Recent Posts

See All

መስከረም 17/2016 በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ።

በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ። ሰራተኞቹ እየታፈኑ ያሉት ደግሞ በውስጥ በተሰገሰጉ የሰው በላው ስርአት ሃይሎች ጥቆማ ሰጭነት መሆኑን ለኢትዮ 360...

መስከረም 17/2016 በሰሜን ሸዋ ሚዳ መርሃቤቴ ላይ ገድይ ያደረገ ህዝባዊ ሃይሉ በዞኑ የተለያዩ አካባቢዎችን ከሰው በላይ ሃይል ነጻማውጣታቸውን ገለጹ

መርጦ ለማርያምን ነጻ ያወጣው ህዝባዊ ሃይል መቅደላ አምባ አምባ ዩኒቨርስቲ ውስጥና በአካባቢው በሚገኝ ካምፕ ውስጥ መሽጎ የነበረውን ይሄንን ሃይል ማጽዳት ተችሏል ብለዋል። አሁን ላይ ከሁሉም አካባቢ የተባረረው ገዳይ...

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ብርጌድ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ። በጎንደር ዙሪያ ማክሰኝት ወረዳ የጭንጫዬ አርሶ...

Email: ethio360dgre@gmail.com

Phone: 540-277-3242

PayPal ButtonPayPal Button

© 2023 by Ethio360 Media

Connect with Us

  • rumble
  • Telegram
  • TikTok

Support Us

Advertise With Us

bottom of page