በአዲስ አበባ በኮዬ ፈጬ አካባቢ ያሉ የ10/90 የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ለሪል እስቴት ይፈለጋሉ በሚል ነዋሪዎቹን ቤታቸውን ሊነጥቋቸው መዘጋጀታቸውን የኢትዮ 360 ምንጮች ገለጹ።
የ10/90 ባለእድሎች 10 በመቶውን ቅድሜያ ከፍለው የቀረውን ደግሞ በየጊዜው ለባንክ እየከፈሉ እንዲኖሩ ለማድረግ የተሰሩ መሆናቸውን ያነሳሉ።
ነዋሪውም የሚጠበቅባቸውን ከከፈለሉ በኋላ ከባንክ የተበደሩትን እዳ በየጊዜው እየከፈሉ በጋራ መኖሪያ ቤቱ መኖር ከጀመሩ ወደ አምስት አመት እንደሆናቸውም ይናገራሉ።
አሁን ግን ሰው በላው ስርአት አምስት አመት ሙሉ ገንዘባቸውን ሲከፍሉ የኖሩበትን ቤታቸውን ሊነጥቃቸው ከዳር ደርሷል ብለዋል።
ነዋሪውን ከገዛ ቤቱ አስወጥቶ በረንዳ ላይ ለመጣል የተዘጋጀው ለሌላ አላማ ሳይሆን ለባለጊዜዎች ሪል እስቴት መገንቢያ በሚል መሆኑንም አመልክተዋል።
በተለይ ባለፉት ሶስት ቀናት ወደ አካባቢው እየተመላለሰ ያለው አካል ነዋሪውን በገዛ ቤቱ ሰላም ነስቶታል ሲሉም ይናገራሉ።
አንዳንዶቹ ደግሞ በአካባቢው ወዳለው አስተዳደር ሔደው አቤት ለማለት ሲሞክሩ የተሰጣቸው ምላሽ ተነሱ ከተባላችሁ ተነሱ ነው በቃ የሚል አምባገነናዊ ምላሽ ነው ይላሉ።
ከዛም አልፎ እንደባለንብረትነታቸውና እንደባለመብት ያማከራቸውም ሆነ ምን እየተካሄደ እንደሆነ እንዲያውቁ ለማድረግ የሞከራ አንዳችም አካል እንደሌለ ይናገራሉ።
ከጋራ መኖሪያ ቤቱ ባለንብረቶች አብዛኞቹ ደግሞ የሚጠበቅባቸውን እዳ ከፍለው የጨረሱ መሆናቸውንም ገልጸዋል።
ነገር ግን ሁሉንም ካልዋጥኩ የሚለው ሰው በላው ስርአት ግን በህጋዊ መንገድ የተሰራውንና በቀድሞ ስርአት የተገነባውን ይሄንን ህንጻ ለማፍረስ ጫፍ ላይ ደርሷል ሲሉም የኢትዮ 360 ምንጮች ገልጸዋል።