top of page

(ኢትዮ 360 - መስከረም 15/2016) በደቡብ ወሎ የአምባሰል ወረዳ ፖሊስ ጽህፈት በህዝባዊ ሃይሉ ተሰበረ።

(ኢትዮ 360 - መስከረም 15/2016) በደቡብ ወሎ የአምባሰል ወረዳ ፖሊስ ጽህፈት በህዝባዊ ሃይሉ ተሰበረ።

በደቡብ ወሎ ዞን ውጫሌ ከተማ የሚገኘው የአምባሰል ወረዳ ፖሊሲ ጽህፈት በህዝባዊ ሃይሉ መሰበሩን የኢትዮ 360 ምንጮች ገለጹ።


ጽህፈት ቤቱን ለማዳን ሲንፈራፈሩ የነበሩ የሆድ አደሩ ብአዴን አድማ ብተናና ሚሊሻ ሙትና ቁስለኛ መሆናቸውንም ሳይጠቁሙ አላለፉም።


ከጥፋታቸው ያልታረሙና ከጠላት ቡድን ጋር በመሆን አሁንም ወገኖቻቸውን በመውጋት ላይ ላሉት የባንዳ ስብስቦችን ህዝባዊ ሃይሉ በተለያዩ መንገዶች ለማስመከር ቢሞርክም ሊሰሙ ባለመቻላቸው ሙትና ቁስለኛ መሆናቸው ቀጥሏል ብለዋል።


ይህ በእንዲህ እንዳለ የአማራ ህዝባዊ ሃይል በዚህ ደረጃ የህልውና ዘመቻ እያደረገ ባለበት ሰዠት አገው በሚል የተሰባሰበ ቡድን ደግሞ አገው ክልልን እመሰርታለሁ በሚል መከራውን እያየ መሆኑን ሳይጠቁሙ አላለፉም።


ሰሞኑን ኢትዮ 360 ባወጣው መረጃ እንጅባራ ዩኒቨርስቲ ውስጥ ያሰለጠነውን ሃይል ሲያስመርቅ እንደነበር ይፋ ማድረጉ ይታወሳል።


በነአበባው ታደሰና ሰማ ጥሩነህ የሚመራው ይሄ ስብስብ አሁን ደግሞ ክልል እመሰርታለሁ ብሎ ብቅ ማለቱንም ምንጮቹ ተናግረዋል።



 
 

Recent Posts

See All
መስከረም 17/2016 በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ።

በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ። ሰራተኞቹ እየታፈኑ ያሉት ደግሞ በውስጥ በተሰገሰጉ የሰው በላው ስርአት ሃይሎች ጥቆማ ሰጭነት መሆኑን ለኢትዮ 360...

 
 
መስከረም 17/2016 በሰሜን ሸዋ ሚዳ መርሃቤቴ ላይ ገድይ ያደረገ ህዝባዊ ሃይሉ በዞኑ የተለያዩ አካባቢዎችን ከሰው በላይ ሃይል ነጻማውጣታቸውን ገለጹ

መርጦ ለማርያምን ነጻ ያወጣው ህዝባዊ ሃይል መቅደላ አምባ አምባ ዩኒቨርስቲ ውስጥና በአካባቢው በሚገኝ ካምፕ ውስጥ መሽጎ የነበረውን ይሄንን ሃይል ማጽዳት ተችሏል ብለዋል። አሁን ላይ ከሁሉም አካባቢ የተባረረው ገዳይ...

 
 
መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ብርጌድ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ። በጎንደር ዙሪያ ማክሰኝት ወረዳ የጭንጫዬ አርሶ...

 
 

Email: ethio360dgre@gmail.com

Phone: 540-277-3242

Donate with PayPal

© 2023 by Ethio360 Media

Connect with Us

  • rumble
  • Telegram
  • TikTok

Support Us

Advertise With Us

bottom of page