top of page

(ኢትዮ 360-መስከረም 16/2016) የመስቀል ደመራና የመውሊድ በአላት በመከበር በላይ ናቸው።


የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የመስቀል ደመራ በአል በሃገር ውስጥና በውጭ በሚገኙ የእምነቱ ተከታዮች ዘንድ በደማቅ ሃይማኖታዊ ስነስርአት በመከበር ላይ ነው።


በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ የእምነቱ አባቶችና ምዕመናን በተገኙበት በደማቅ ስነስርአት እየተከበረ ያለው ይሄው በአላ በተለያዩ የሃገሪቱ ክፍሎችም ፍጹም ሃይማኖታዊ ጨዋነት በተላበሰ መልኩ እየተከበረ መሆኑንም የኢትዮ 360 ምንጮች አንስተዋል።


የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ በየትም አካባቢ እንዳይውለበለብ ለማድረግ ሲለፋ የነበረው የሰው በላው ስብስብ ያሰበውን ያህል እቅዱን ሊያሳካ አልቻለም ሲሉም ተናግረዋል።



በፍጹም ሃይማኖታዊ ጨዋነቱ የሚታወቁት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ምእመናንም ባህላዊ አላባሳትን በመልበስ ለበአሉ ትልቅ ግርማ ሞገስን ሰተውታል ብለዋል።



ይህ በእንዲህ እንዳለ 1 ሺህ 498ኛው የመውሊድ በዓል በታላቁ አንዋር መስጅድ በተለያዩ ሃይማኖታዊ ዝግጅቶች በመከበር ላይ መሆኑንም የኢትዮ 360 ምንጮች አስታውቀዋል።



የመውሊድ በዓል የነቢዩ መሐመድ መልካም ተግባራትን በማሰብና የተለያዩ ሃይማኖቱ የሚፈቅደውን ተግባር በመፈጸም የሚከበር በአል መሆኑንም አስታውሰዋል።



Recent Posts

See All

መስከረም 17/2016 በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ።

በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ። ሰራተኞቹ እየታፈኑ ያሉት ደግሞ በውስጥ በተሰገሰጉ የሰው በላው ስርአት ሃይሎች ጥቆማ ሰጭነት መሆኑን ለኢትዮ 360...

መስከረም 17/2016 በሰሜን ሸዋ ሚዳ መርሃቤቴ ላይ ገድይ ያደረገ ህዝባዊ ሃይሉ በዞኑ የተለያዩ አካባቢዎችን ከሰው በላይ ሃይል ነጻማውጣታቸውን ገለጹ

መርጦ ለማርያምን ነጻ ያወጣው ህዝባዊ ሃይል መቅደላ አምባ አምባ ዩኒቨርስቲ ውስጥና በአካባቢው በሚገኝ ካምፕ ውስጥ መሽጎ የነበረውን ይሄንን ሃይል ማጽዳት ተችሏል ብለዋል። አሁን ላይ ከሁሉም አካባቢ የተባረረው ገዳይ...

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ብርጌድ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ። በጎንደር ዙሪያ ማክሰኝት ወረዳ የጭንጫዬ አርሶ...

Email: ethio360dgre@gmail.com

Phone: 540-277-3242

PayPal ButtonPayPal Button

© 2023 by Ethio360 Media

Connect with Us

  • rumble
  • Telegram
  • TikTok

Support Us

Advertise With Us

bottom of page