top of page

(ኢትዮ 360-ሰኔ 21/2015)በምስራቅ ጎጃም ደብረወርቅ ከተማ የኦህዴዱ ሃይል አንድ ሴትን ገሎ በርካቶችን አቆሰለ።


በምስራቅ ጎጃም እናርጅ እናውጋ ወረዳ የደብረወርቅ ከተማን ለማስከፈት ተኩስ የከፈተው የኦህዴዱ መከላከያ ሃይል አንድ ሴት ገሎ በርካቶችን ማቁሰሉን የኢትዮ 360 ምንጮች ገለጹ።


ይህው ሃይል ከወረዳው ፖሊስ ጋር በመተባበር ለወረዳው ጤና ጣቢያ አገልግሎት የሚውሉ አንቡላንሶችን ለመጠቀም የአንቡላንሶችን ሹፌሮች መሳሪያ በመደቀንና በማስገደድ ከየቤታቸው አፍኖ እንደወሰዳቸውም ይናገራሉ።


በወረዳው ያሉ ሁሉንም አንቡላሶች ወደ ፖሊስ ጣቢያ እንዲወሰዱ ማድረጉንም ነው ምንጮቹ ያመለከቱት።


እነዚህን አምቡላንሶች በአንድ ላይ ተሰባስበው የተወሰዱት ለሌላ ጉዳይ ሳይሆን በንጹሃን ላይ ጥቃት ለመፈጸሚያ ብቻ ነው ሲሉ እየተሰራ ያለውን ወንጀል አጋልጠዋል።


በአምቡላንስ ሲንቀሳቀሱ የፋኖ ህዝባዊ ሃይልም ሆነ ማህበረተሰቡ አያውቅም ስለዚህም በቀላሉ ጥቃት ለመፈጸም ያስችለናል የሚለው ደግሞ በአካባቢው ፖሊስ ጭምር ምክር የተሰጠበው ነው ሲሉ የታሰበውን ተንኮል ያጋልጣሉ።


የፋኖ ህዝባዊ ሃይልን ፊት ለፊት መግጠም ያልቻለው የኦህዴዱ ስብስብና የአካባቢው ሆድ አደር ካድሬ ትናንት በሽማግሌ ሰላም እንደወረደ አስመስለው ፋኖ አዱኛው ፍቃዱን ሲያስበሉ አሁን ደግሞ በአንቡላስ ወላድ ወይንም ህመምተኛ መስለው የደብረወርቅ ፋኖን ለማጥቃት ዝግጅታቸውን አጠናቀዋል ብለዋል።


በምስራቅ ጎጃም ደብረወርቅ ከተማ እና አካባቢው ላይ የኦህዴድ ሃይል በንፁሀን አርሶ አደሮች እና ህፃናት ላይ የጀመረውን የዘር ማጥፋት ወንጀል በክልሉ በሁሉም አካባቢዎች እየፈጸመው ነው ሲሉ የኢትዮ 360 ምንጮች ተናግረዋል።


Recent Posts

See All

መስከረም 17/2016 በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ።

በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ። ሰራተኞቹ እየታፈኑ ያሉት ደግሞ በውስጥ በተሰገሰጉ የሰው በላው ስርአት ሃይሎች ጥቆማ ሰጭነት መሆኑን ለኢትዮ 360...

መስከረም 17/2016 በሰሜን ሸዋ ሚዳ መርሃቤቴ ላይ ገድይ ያደረገ ህዝባዊ ሃይሉ በዞኑ የተለያዩ አካባቢዎችን ከሰው በላይ ሃይል ነጻማውጣታቸውን ገለጹ

መርጦ ለማርያምን ነጻ ያወጣው ህዝባዊ ሃይል መቅደላ አምባ አምባ ዩኒቨርስቲ ውስጥና በአካባቢው በሚገኝ ካምፕ ውስጥ መሽጎ የነበረውን ይሄንን ሃይል ማጽዳት ተችሏል ብለዋል። አሁን ላይ ከሁሉም አካባቢ የተባረረው ገዳይ...

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ብርጌድ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ። በጎንደር ዙሪያ ማክሰኝት ወረዳ የጭንጫዬ አርሶ...

bottom of page