top of page

(ኢትዮ 360-ሰኔ 21/2015) በአፋር ክልል ወጣቶች በገፍ እየታፈኑ ነው።


በአፋር ክልል የብልጽግናውን አስተዳደር ይቃወማሉ የተባሉ ወጣቶች ሁሉ በገፍ እየታሰሩ መሆኑን የኢትዮ 360 ምንጮች ገለጹ።


በማህበራዊ ድረገጽ ላይ ስርአቱን የሚቃወሙ ጽሁፎችን ሼርና ላይክ የሚያደርጉ ሁሉ የዚህ አፈና ሰለባ እየሆኑ ነው ብለዋል።


እስካሁንም ቀአስ መሃመድ፣አሊ ሁሴን፣ሐሰን ሁሴን፣መሃመድ ሐሰንና በርካታ ቁጥር ያላቸው ወጣቶች በተለያዩ እስር ቤቶች ታፍነው እንደሚገኙም ገልጸዋል።


ክልሉን እመራለሁ የሚለው አካል እስከ ታችኛው ካድሬ በመተባበር በዋናነት እነዚህን ወጣቶች አሳሪና አሳሳሪ መሆኑን ይናገራሉ።


ሰሞኑን በተከታታይ በአፋር ንጹሃን ዜጎች ላይ የኦህዴዱ መከላከያ ሃይል የፈጸመውን ጥቃት ተከትሎ ስለተገደሉት ንጹሃን ወገኞቻቸው የጻፉም ሆኑን ጽሁፉን ለሌላ ያጋሩ በሙሉ በዚሁ አካል እየተሳደዱና እየታፈኑ መሆኑን ይናገራሉ።


አፈናና እስሩ በየቀኑና በየሰአቱ ከመሆኑ ጋር ተያይዞም ምን ያህል ወጣቶች እነዳፈኑ ማወቅ እንዳልተቻለም ምንጮቹ አመልክተዋል።


የእያንዳንዱ የመንግስት ሰራተኛ ስልክ በመጥለፍ ጭምር ብርበራ የሚያካሂደው የክልሉ አስተዳደር በየመንገዱ የሚያገኘውን ወጣትም ስልክ ካልፈተሽኩ በሚል ስራ በዝቶበታል ብለዋል።


በአፋር ክልል ያለው አፈናና ማሳደድ ከኑሮው ጋር ተጨምሮ የህዝቡን መከራ አብዝቶታል ብለዋል የኢትዮ 360 ምንጮች።



Recent Posts

See All

መስከረም 17/2016 በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ።

በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ። ሰራተኞቹ እየታፈኑ ያሉት ደግሞ በውስጥ በተሰገሰጉ የሰው በላው ስርአት ሃይሎች ጥቆማ ሰጭነት መሆኑን ለኢትዮ 360...

መስከረም 17/2016 በሰሜን ሸዋ ሚዳ መርሃቤቴ ላይ ገድይ ያደረገ ህዝባዊ ሃይሉ በዞኑ የተለያዩ አካባቢዎችን ከሰው በላይ ሃይል ነጻማውጣታቸውን ገለጹ

መርጦ ለማርያምን ነጻ ያወጣው ህዝባዊ ሃይል መቅደላ አምባ አምባ ዩኒቨርስቲ ውስጥና በአካባቢው በሚገኝ ካምፕ ውስጥ መሽጎ የነበረውን ይሄንን ሃይል ማጽዳት ተችሏል ብለዋል። አሁን ላይ ከሁሉም አካባቢ የተባረረው ገዳይ...

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ብርጌድ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ። በጎንደር ዙሪያ ማክሰኝት ወረዳ የጭንጫዬ አርሶ...

Email: ethio360dgre@gmail.com

Phone: 540-277-3242

Donate with PayPal

© 2023 by Ethio360 Media

Connect with Us

  • rumble
  • Telegram
  • TikTok

Support Us

Advertise With Us

bottom of page