top of page

(ኢትዮ 360-ሰኔ 21/2015)አንድ ከፍተኛ የአፍሪከ ዲፕሎማት በኦነግ ታገቱ።



አንድ ከፍተኛ የአፍሪከ ዲፕሎማት በኦነግ ገዳይ ቡድን መታገታቸውም የኢትዮ 360 የውስጥ ምንጮች ገለጹ።


በከፍተኛ ሚስጥር እንዲያዝ የተደረገውን ይሄውንን ጉዳይ በዋናነት ውስጥ ለውስጥ በሚስጥር ለመጨረስ እየሰሩ ያሉት ደግሞ የውጭ ጉዳይ እና የደህንነት ቢሮው የውጭ መምሪያ ክፍሎች መሆናቸውን ይናገራሉ።


የየትኛው የአፍሪካ ሃገር ዲፕሎማት እንደሆኑ ማወቅ ያልተቻለውን ግለሰብ ለማስለቀቅ ደግሞ የኦነጉ ቡድን ከፍተኛ የዶላር መጠን መጠየቁን አመልክተዋል።


አዲስ አበባ አካባቢው ለስራ ከሔዱበት ወደ ኤምባሲያቸው ሲመለሱ የታገቱት አፍሪካ ሃገር ዲፕሎማት እገታ ጋር በተያያዘ ቤተመንግስቱን የተቆጣጠረው አካል እጁ ኣይኖርበት አልቀረም ሲሉም ግምታቸውን አስቀምጠዋል።


ከአንድ ቀን በፊት የታገቱትን ዲፕሎማት ለማስለቀቅ ብር ሳይሆን ከፍተኛ የዶላር መጠን የጠየቀው ይሄው የገዳዮች ስብስብ ሰሞኑን አዲስ አበባ አቃቂ ቃሊቲና ሃና ማሪያም አካባቢው መታየቱን ኢትዮ 360 በመረጃው ማውጣቱን ያስታውሳሉ።


እስካሁን ድረስ ስለዲፕሎማቱ እገታ ከኤምባሲውም ይሁን ኢትዮጵያን አስተዳድራለሁ ከሚለው አካል አንዳችም የወጣ መረጃ እንዳይኖር ለማድርግ በከፍተኛ ጥንቃቄና ሚስጥር እየተሰራ መሆኑንም የውስጥ ምንጮቹ ይናገራሉ።


 
 

Recent Posts

See All
መስከረም 17/2016 በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ።

በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ። ሰራተኞቹ እየታፈኑ ያሉት ደግሞ በውስጥ በተሰገሰጉ የሰው በላው ስርአት ሃይሎች ጥቆማ ሰጭነት መሆኑን ለኢትዮ 360...

 
 
መስከረም 17/2016 በሰሜን ሸዋ ሚዳ መርሃቤቴ ላይ ገድይ ያደረገ ህዝባዊ ሃይሉ በዞኑ የተለያዩ አካባቢዎችን ከሰው በላይ ሃይል ነጻማውጣታቸውን ገለጹ

መርጦ ለማርያምን ነጻ ያወጣው ህዝባዊ ሃይል መቅደላ አምባ አምባ ዩኒቨርስቲ ውስጥና በአካባቢው በሚገኝ ካምፕ ውስጥ መሽጎ የነበረውን ይሄንን ሃይል ማጽዳት ተችሏል ብለዋል። አሁን ላይ ከሁሉም አካባቢ የተባረረው ገዳይ...

 
 
መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ብርጌድ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ። በጎንደር ዙሪያ ማክሰኝት ወረዳ የጭንጫዬ አርሶ...

 
 

Email: ethio360dgre@gmail.com

Phone: 540-277-3242

Donate with PayPal

© 2023 by Ethio360 Media

Connect with Us

  • rumble
  • Telegram
  • TikTok

Support Us

Advertise With Us

bottom of page