top of page

(ኢትዮ 360 - ሰኔ 21/2015) የግል ባንኮች ከፍተኛ የሆነ የጥሬ ገንዘብ እጥረት ገጠማቸው።


በኢትዮጵያ በሚገኙ የግል ባንኮች ከፍተኛ የሆነ የጥሬ ገንዘብ እጥረት የተከሰተው ሁሉም የግል ባንኮች ከ5 ቢሊዮን ያላነሰ ጥሬ ገንዘብ በመሰብሰብ ትግራይ ክልል ወደአሉ ቅርንጫፎች እንዲልኩ በመደረጉ ነው ሲሉ የኢትዮ 360 የውስጥ ምንጮች አስታወቁ።


ይሄ የተደረገው ደግሞ የፕሪቶሪያው ስምምነት ተደረገ በተባለ ማግስት መሆኑንም ሳይጠቁሙ አላለፉም።


ከዚህ ጋር ተያያዞ ከፍተኛ የጥሬ ገንዘብ እጥረት የገጠማቸው የግል ባንኮች ታይቶና ተሰምቶ በማይታወቅ ሁኔታ ከደንበኞቻቸው ጋር ዱላ ቀረሽ ንትርክ እና ጭቅጭቅ ውስጥ መግባታቸውንም ያነሳሉ።


ሰራተኛው ይሄ ነገር ከአቅሙ በላይ ስለሆነ የዚህ የጥሬ ገንዘብ እጥረት ምክንያት ምን እንደሆነ የበላይ ሃላፊዎችን በማነጋገር ጭምር ለማጣራት ከፍተኛ ትግል እያደረገ መሆኑንም አመልክተዋል።


እንደእውነቱ ከሆነ ይላሉ ምንጮቹ ብሩ ትግራይ ክልልም ቢሆን የሄደው ገንዘቡ ወደ ባንክ ቀጥታ ከሆነ የገባው ከባንክ ስርዓት ስላልወጣ የገንዘብ እጥረቱ አይፈጠርም ነበር ሲሉም ጥርጣሬያቸውን ያስቀምጣሉ።


ከዚህ በመነሳትም የግል ባንኮቹ ወደ ትግራይ ላኩ የተባለው በቢሊየን የሚቆጠር ብር አንድም መንግስት ነኝ የሚለው አካል አላከውም ካልሆነም እዛ ከደረሰ በኋላ ወደ ባንክ እንዳይገባ ተደርጓል ማለት ሲሉም ምንጮቹ እየተሰራ ያለውን ስርአታዊ ወንጀል ያጋልጣሉ።


የግን ባንኮቹ አሁን ላይ ለግለሰብም ሆነ ለድርጅቶች የሚሰጡት የገንዘብ አቅም በየቀኑ እየቀነሰና የለም ወደሚባል ደረጃ እየተሸጋገረ መሆኑንም ሳይጠቁሙ አላለፉም።

Recent Posts

See All

መስከረም 17/2016 በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ።

በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ። ሰራተኞቹ እየታፈኑ ያሉት ደግሞ በውስጥ በተሰገሰጉ የሰው በላው ስርአት ሃይሎች ጥቆማ ሰጭነት መሆኑን ለኢትዮ 360...

መስከረም 17/2016 በሰሜን ሸዋ ሚዳ መርሃቤቴ ላይ ገድይ ያደረገ ህዝባዊ ሃይሉ በዞኑ የተለያዩ አካባቢዎችን ከሰው በላይ ሃይል ነጻማውጣታቸውን ገለጹ

መርጦ ለማርያምን ነጻ ያወጣው ህዝባዊ ሃይል መቅደላ አምባ አምባ ዩኒቨርስቲ ውስጥና በአካባቢው በሚገኝ ካምፕ ውስጥ መሽጎ የነበረውን ይሄንን ሃይል ማጽዳት ተችሏል ብለዋል። አሁን ላይ ከሁሉም አካባቢ የተባረረው ገዳይ...

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ብርጌድ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ። በጎንደር ዙሪያ ማክሰኝት ወረዳ የጭንጫዬ አርሶ...

Email: ethio360dgre@gmail.com

Phone: 540-277-3242

Donate with PayPal

© 2023 by Ethio360 Media

Connect with Us

  • rumble
  • Telegram
  • TikTok

Support Us

Advertise With Us

bottom of page