top of page

ኢትዮ 360 - ነሀሴ 10/2015)በምዕራብ ወሎ ጃማ ደጎሎ የሚዳ ህዝባዊ ሃይል የገዳዩን ስርአት ሃይል ከጥቅም ውጪ አደረገው።


ከሁለት ቀን በፊት ይላሉ ለዚሁ ገዳይ ቡድን ያደረው የክልሉ ሚሊሻ በጣለው ቦንብ የህዝባዊ ሃይሉ አባላት ላይ ጉዳት አድርሶ እንደነበር ይናገራሉ።


ነገር ግን ይሄንን ግድያ ተጠቅሞ የኦህዴዱ ሃይል ወደ ከተማ ለማለፍ ያደረገው ሙከራ በህዝባዊ ሃይሉ ከሽፎበታል፣ጀማ ላይ ማረፊያ አድርጎት የነበረውን ካምፕም ከጥቅም ውጪ አድርጎታል ከ2ሺ በላይ የኦህዴዱ ሃይልም ተገሏል ብለዋል።


ህዝባዊ ሃይሉ ሙትና ቁስለኛ ካደረጋቸውም ሌላ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሃይል ማርኳል፣የግልና የቡድን መሳሪያዎችንም ማርኳል ሲሉ ለኢትዮ 360 ገልጸዋል።


ደብረብርሃን ላይ የሚንቀሳቀሰው ሃይል ደግሞ መንገድ በመዝጋት ጭምር በአካባቢው ምንም አይነት እንቅስቃሴ እንዳይኖር ማድረጉንም ተናግረዋል።


ይሄ ደግሞ ደብረብርሃን ላይ ያለን ሃይል ለማዛወር ቢሆንም አይሳካላትም ሲሉ እውነቱን ተናግረዋል።

ደብረብርሃን ላይ ከሶማሊያ አምጥቶ ያፈሰሰው የኦህዴድ ሃይል ደግሞ በኮሌራ ወረርሽኝ ተይዞ ሁለት ሆስፒታሎችን ሞልቷል ሲሉ የህዝባዊ ሃይሉ አባላት ይናገራሉ።


አባላቱ ከህመሙ የተነሳ በእግራቸው መንቀሳቀስ በማይችሉበት ሁኔታ መታመማቸው ነው ለኢትዮ 360 የገለጹት።


Recent Posts

See All

መስከረም 17/2016 በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ።

በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ። ሰራተኞቹ እየታፈኑ ያሉት ደግሞ በውስጥ በተሰገሰጉ የሰው በላው ስርአት ሃይሎች ጥቆማ ሰጭነት መሆኑን ለኢትዮ 360...

መስከረም 17/2016 በሰሜን ሸዋ ሚዳ መርሃቤቴ ላይ ገድይ ያደረገ ህዝባዊ ሃይሉ በዞኑ የተለያዩ አካባቢዎችን ከሰው በላይ ሃይል ነጻማውጣታቸውን ገለጹ

መርጦ ለማርያምን ነጻ ያወጣው ህዝባዊ ሃይል መቅደላ አምባ አምባ ዩኒቨርስቲ ውስጥና በአካባቢው በሚገኝ ካምፕ ውስጥ መሽጎ የነበረውን ይሄንን ሃይል ማጽዳት ተችሏል ብለዋል። አሁን ላይ ከሁሉም አካባቢ የተባረረው ገዳይ...

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ብርጌድ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ። በጎንደር ዙሪያ ማክሰኝት ወረዳ የጭንጫዬ አርሶ...

Email: ethio360dgre@gmail.com

Phone: 540-277-3242

PayPal ButtonPayPal Button

© 2023 by Ethio360 Media

Connect with Us

  • rumble
  • Telegram
  • TikTok

Support Us

Advertise With Us

bottom of page