ኢትዮ 360 - ነሀሴ 4/2015) የ12ኛ ክፍል መለቀቂያ ፈተና በወሰዱ ተማሪዎች ላይ የተፈጸመው ግፍ ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ሊጋለጥ ይገባል።
- Ethio 360 Media 2
- Aug 10, 2023
- 1 min read
በ12ኛ ክፍል መለቀቂያ ፈተና በወሰዱ ተማሪዎች ላይ የተፈጸመው ግፍ ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ሊጋለጥ የገባል ሲሉ የኢትዮ ምንጮች ገለጸዋል።
ወንዶች በከባድ ተደብድበዋል፣ሴቶች ተደፍረዋል፣ በፍተሻ ሰበብ ቤተሰብ የሰጣቸው ገንዘብ ሰው በላው ስርአት ባሰማራው ሃይል እንዲሰርቁ ተደርገዋል ይላሉ።
ኢትዮ 360 በቅርቡ ባወጣው መረጃም የተረጃ ልጆች በሚል ተለይተው እንዲፈተኑ ለተደረጉት ተማሪዎች አንድ አስተማሪ ተመድቦ ለጥያቄዎቹ መልስ ሲሰጥ መቆየቱን ይፋ ማድረጉ ይታወሳል።
በአንጻሩ ደግሞ ለብዙሃኑ ተማሪ ሶስት ፈታኞችን መድቦ የነበረው አካል በነዚሁ ተመደቡ በተባሉት መምህራን አማካኝነት ተማሪዎች እንዲፈሩ ሲደረጉ፣ሲረበሹ ሰአታቸውን ሳይጨርሱ ፈተና ሲነጠቁ መቆየታቸውንም ኢትዮ 360 በመረጃዊ ሲያጋልጥ ቆይቷል።
በቃሊቲ አካባቢ ለፈተና የተመደቡ ተማሪዎች ላይ የደረሰው ግን ሊናገሩትና ሊሰሙት የሚከብድ ነው ሲሉም ምንጮቹ ይናገራሉ።
በቅርቡ ኢትዮ 360 ያናገራቸው የተፈታኝ ተማሪዎች ወላጆች ይሄንን ግፍ የፈጸመው ብርሃኑ ነጋ በአለም አቀፉ ወንጀለኞች ፍርድ ቤት ይቅረብልን ሲሉ መጠየቃቸው ይታወሳል።