top of page

(ኢትዮ 360 -ግንቦት 1/2015) በአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ከፍተኛ የገንዘብ ምዝበራ እየተካሄደ ነው።


በአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ታክስ የማይክፈልበት በሚል ከፍተኛ ገንዘብ እየተመዘበረ መሆኑን የኢትዮ 360 ምንጮች ገለጹ።


በተለይ በየክፍለ ከተሞች አዳዲስ ሹመት በመስጠት ስም የሚወጣው ገንዘብ ከፍተኛ መሆኑን ያስቀምጣሉ።


ለሌብነት እንዲያመቻቸው በአንድ ክፍለ ከተማ በትንሹ አራት የቢሮ ሃላፊ እንዲመደብ ይደርጋል ይላሉ።


ለነዚህ የቢሮ ሃላፊዎች በመደበኛነት የሚከፈለው ገንዘብ እንዳለ ሆኖ ለእያንዳንዱ ታክስ የማይከፈለበት 16ሺ ብር እንዲመደብላቸው እንደሚደረግም ይናገራሉ።


16ሺ ብሩ ከታክስ ውጪ በሚል ሲመደብላቸው ምክንያት ተደርጎ የሚቀመጠው ደግሞ ለቤት ኪራይ የሚል መሆኑንም ያነሳሉ።


ለአራት ቢሮ ሃላፊዎች በአንድ ጊዜ 64ሺ ብር ወጪ እንደሚደረግ የሚያነሱት ምንጮቹ ይሄ ደግሞ በየክፍለከተማ ባሉት አመራሮች ልክ ሲታሰብ ደግሞ በሚሊየን የሚቆጠር ብር ከየክፍለ ከተማው በጀት መሰረቁን ያሳያል ይላሉ።


ለአራት ቢሮ ሃላፊዎች ይባል እንጂ በየጊዜው በየቦታው የሚሾመው አመራር ከፍተኛ ስለሆነ የገንዘቡም መጠን በዛው ልክ ይጨምራል ሲሉም የኢትዮ 360 ምንጮች ገልጸዋል።

Recent Posts

See All

መስከረም 17/2016 በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ።

በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ። ሰራተኞቹ እየታፈኑ ያሉት ደግሞ በውስጥ በተሰገሰጉ የሰው በላው ስርአት ሃይሎች ጥቆማ ሰጭነት መሆኑን ለኢትዮ 360...

መስከረም 17/2016 በሰሜን ሸዋ ሚዳ መርሃቤቴ ላይ ገድይ ያደረገ ህዝባዊ ሃይሉ በዞኑ የተለያዩ አካባቢዎችን ከሰው በላይ ሃይል ነጻማውጣታቸውን ገለጹ

መርጦ ለማርያምን ነጻ ያወጣው ህዝባዊ ሃይል መቅደላ አምባ አምባ ዩኒቨርስቲ ውስጥና በአካባቢው በሚገኝ ካምፕ ውስጥ መሽጎ የነበረውን ይሄንን ሃይል ማጽዳት ተችሏል ብለዋል። አሁን ላይ ከሁሉም አካባቢ የተባረረው ገዳይ...

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ብርጌድ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ። በጎንደር ዙሪያ ማክሰኝት ወረዳ የጭንጫዬ አርሶ...

bottom of page