top of page

(ኢትዮ 360-ግንቦት 3/2015) በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ራሱን አጥፍቷል በሚል የተሳሳተ መረጃ ሲወጣበት የነበረው ተማሪ አባባው ስንሻው አራት ቦታ በስለት



በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ራሱን አጥፍቷል በሚል የተሳሳተ መረጃ ሲወጣበት የነበረው ተማሪ አባባው ስንሻው አራት ቦታ በስለት መወጋቱን የኢትዮ 360 የዩኒቨርስቲው ምንጮች ገለጹ።


ከአንድ ቀን በፊት ኢትዮ 360 ባወጣው መረጃ ዩኒቨርስቲው ተማሪ አበባው ራሱን ገሎ ነው ሲል ያወጣው መረጃ ከእውነት የራቀ መሆኑን ማጋለጡ ይታወሳል።


ነገር ግን ተማሪ አበባው ራሱን ገሎ ሳይሆን ሆን ተብሎ መገደሉንና ከተገደለም በኋላ ከዶርም ውጪ በሚገኘውና ቆርቆሮ በቆርቆሮ በተሰራው መጸዳጃ ቤት እራሱን አጥፍቶ እንዲገኝ መደረጉን ይፋ አድርጓል።


አሁንም የኢትዮ 360 የዩኒቨርስቲው የውስጥ ምንጮች ተማሪ አበባው አራት ቦታ በጩቤ መወጋቱንና ሰውነቱ በሙሉ ደምበደም ሆኖ መታየቱንም አጋልጠዋል።


ተማሪ አበባው በስለት የተወጋው አንገቱና ጎኑ ላይ መሆኑንም ጠቁመዋል።


አሁንም የተማሪውን ጉዳይ በትክክል ማጣራት ያልፈለገው የዩኒቨርስቲው አስተዳደር በኦህዴዱ የጸጥታ ሃይል የአማራ ተማሪዋችን በሌሊት እያሳፈነና እያስደበደበ ነው።


ትናንት ከምሽቱ 3:00 ሰአት አካባቢ ግቢው ውስጥ ካለው ሀበሻ ካፌ ራት አሰርተው ይዘው ሲመጡ የተደበደቡ ሴት ተማሪዋች ሆስፒታል መግባታቸውንም ነው የዩኒቨርስቲው የውስጥ ምንጮች የሚናገሩት።


በድብደባ ብዛት መንቀሳቀስ ያልቻሉ ተማሪዎች ያለምንም ህክምና በዶርማቸው ተኝተው እንደሚገኙም ሳይጠቁሙ አላለፉም።


ወደ ቤተመጻህፍት ሲሄዱም ሆነ በየዶርማቸው ያሉ የአማራ ተወላጆች ሁሉ በዚሁ ሃይል የሚደርስባቸው ማሳደድና ድብደባ አሁንም መቀጠሉን ምንጮቹ ተናግረዋል።

Recent Posts

See All

መስከረም 17/2016 በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ።

በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ። ሰራተኞቹ እየታፈኑ ያሉት ደግሞ በውስጥ በተሰገሰጉ የሰው በላው ስርአት ሃይሎች ጥቆማ ሰጭነት መሆኑን ለኢትዮ 360...

መስከረም 17/2016 በሰሜን ሸዋ ሚዳ መርሃቤቴ ላይ ገድይ ያደረገ ህዝባዊ ሃይሉ በዞኑ የተለያዩ አካባቢዎችን ከሰው በላይ ሃይል ነጻማውጣታቸውን ገለጹ

መርጦ ለማርያምን ነጻ ያወጣው ህዝባዊ ሃይል መቅደላ አምባ አምባ ዩኒቨርስቲ ውስጥና በአካባቢው በሚገኝ ካምፕ ውስጥ መሽጎ የነበረውን ይሄንን ሃይል ማጽዳት ተችሏል ብለዋል። አሁን ላይ ከሁሉም አካባቢ የተባረረው ገዳይ...

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ብርጌድ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ። በጎንደር ዙሪያ ማክሰኝት ወረዳ የጭንጫዬ አርሶ...

Email: ethio360dgre@gmail.com

Phone: 540-277-3242

PayPal ButtonPayPal Button

© 2023 by Ethio360 Media

Connect with Us

  • rumble
  • Telegram
  • TikTok

Support Us

Advertise With Us

bottom of page