top of page

(ኢትዮ 360 -ግንቦት 30/2015) አርበኛ ዘመነ ካሴ በድጋሚ ሊታሰር ነው።


ፌደራል ላይ የተቀመጠው አካል በድጋሚ አርበኛ ዘመነ ካሴን ለማሰር እንቅስቃሴ ላይ መሆኑን የኢትዮ 360 ምንጮች አስታወቁ።


የብአዴኑ ብልጽግና አርበኛ ዘመነ ካሴ ላይ እስከአሁን የፈጠራቸው የሀሰት ክሶች በሕግ ፊት ከሽፈውና ሀሰትነታቸውም ተረጋግጦ፤ ከዘጠኝ ወራት የፖለቲካ እስራት በኋላ አርበኛ ዘመነ ካሴ ከባሕር ዳር ማረሚያ ቤት የወጣው ከሁለት ቀን በፊት ግንቦት 28 ቀን 2015 ዓ.ም እንደነበርም ምንጮቹ ያስታውሳሉ።


የዘመነ ካሴን የሃሰት ክስ ሲመለከቱ የቆዩት የክልሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኞችም በዚህ ጉዳይ ላይ አርበኛ ዘመነ ካሴን መክሰስ አንችልም፤ ተገቢም አይደለም፤ ይሄን ጉዳይ በተደጋጋሚ ስለተመለከትነው ፍርድ ለመስጠት አንቀመጥም የሚል ቁርጥ ያለ ውሳኔ ማሳለፋቸውም የተሰማሁ በነዚሁ ቀናቶች እንደነበር ያነሳሉ።


የክልሉ ከፍተኛ ዳኞች አቋም ያናደደው የኦህዴዱ ስብስብም ፌደራል ላይ እንደ አዲስ ክሱን በማቅረብ ለአርበኛ ዘመነ ካሴ መጥሪያ ለመስጠት እየተረባረቡ መሆኑንም ሳይጠቁሙ አላለፉም።


ለአርበኛው የመጥሪያ ወረቀት መስጠት ብቻ ሳይሆን አፍኖ ለመውሰድም እቅድ መያዙን ጠቁሙዋል።


አርበኛ ዘመነ ካሴ ከእስር መውጣትን ተከትሎ ከህዝቡ የተሰጠውን ምላሽ ያየውና በፍርሃት እየራደ ያለው አብይ አህመድ በተቻለ አቅም ሁሉ እስክንድር ነጋንና አርበኛ ዘመነ ካሴን ለማጥፋት እንቅልፉን ማጣቱን ምንጮቹ ይናገራሉ።


ከዚህ ፍርሃቱ ለመውጣቱም ሰሞኑን እስክንድር ነጋ እንዲገደል ትእዛዝ ሲያሳልፍ አሁን ደግሞ አብረኛ ዘመነን አፍኖ ወደ ፌደራል ለመውሰድ ካልሆነም ለመግደል መመሪያ አውርዷል ሲሉ የኢትዮ 360 ምንጮች ተናግረዋል።

Recent Posts

See All

መስከረም 17/2016 በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ።

በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ። ሰራተኞቹ እየታፈኑ ያሉት ደግሞ በውስጥ በተሰገሰጉ የሰው በላው ስርአት ሃይሎች ጥቆማ ሰጭነት መሆኑን ለኢትዮ 360...

መስከረም 17/2016 በሰሜን ሸዋ ሚዳ መርሃቤቴ ላይ ገድይ ያደረገ ህዝባዊ ሃይሉ በዞኑ የተለያዩ አካባቢዎችን ከሰው በላይ ሃይል ነጻማውጣታቸውን ገለጹ

መርጦ ለማርያምን ነጻ ያወጣው ህዝባዊ ሃይል መቅደላ አምባ አምባ ዩኒቨርስቲ ውስጥና በአካባቢው በሚገኝ ካምፕ ውስጥ መሽጎ የነበረውን ይሄንን ሃይል ማጽዳት ተችሏል ብለዋል። አሁን ላይ ከሁሉም አካባቢ የተባረረው ገዳይ...

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ብርጌድ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ። በጎንደር ዙሪያ ማክሰኝት ወረዳ የጭንጫዬ አርሶ...

Email: ethio360dgre@gmail.com

Phone: 540-277-3242

PayPal ButtonPayPal Button

© 2023 by Ethio360 Media

Connect with Us

  • rumble
  • Telegram
  • TikTok

Support Us

Advertise With Us

bottom of page