top of page

(ኢትዮ 360 - ጳጉሜ 1/2015) በጋምቤላ ማጃንግ ዞን ጎደሬ ወረዳ በአማራ ተወላጆች ላይ የተጀመረው ጥቃት ቀጥሏል።


በጋምቤላ ማጃንግ ዞን ጎደሬ ወረዳ በአማራ ተወላጆች ላይ የተጀመረው ጥቃት ዛሬም ተጠናክሮ መቀጠሉን የኢትዮ 360 ምንጮች ገልጹ።


በዚህ ጥቃት እስካሁን ሰባት ሰዎች መገደላቸው ቢታወቅም ነገር ግን ጥቃቱ በተለያዩ አካባቢዎች ከመፈጸሙ ጋር ተያይዞ የሟቾቹ ቁጥር ከዚህም በላይ ሊጨምር እንደሚችልም አመልክተዋል።


ከዚህ ጥቃት ጋር ተያይዞ በርካታ የአማራ ተወላጆች ከመጎዳታቸው ጋር ተያይዞም የተጎጂዎቹን ቁጥር በትክክል ማወቅ አለመቻሉንም ምንጮቹ ገልጸዋል።


በተደጋጋሚ በክልሉ የሚፈጸመው ይሄንን አይነቱን ጥቃት የትኛውም አካል ሊያስቆመው ባለመቻሉ አሁንም በንጹሃን ዜጎች ላይ የሚፈጸመው ግድያ ቀጥሏል ሲሉ ምንጮቹ ተናግረዋል።


 
 

Email: ethio360dgre@gmail.com

Phone: 540-277-3242

Donate with PayPal

© 2023 by Ethio360 Media

Connect with Us

  • rumble
  • Telegram
  • TikTok

Support Us

Advertise With Us

bottom of page