top of page

(ኢትዮ 360_ግንቦት 1/2015)በድሬደዋ የሚገኙ የህክምና ባለሙያዎች የመደመር መጽሃፍን በ1ሺ ብር ግዙ ተባሉ።


በድሬደዋ የሚገኙ የህክምና ባለሙያዎች የአብይ አህመድን የመደመር መጽሃፍ በ1ሺ ብር እንዲገዙ መገደዳቸውን ለኢትዮ 360 ገለጹ።


በተለይ የድሬደዋ ሪፈራል ሆስፒታል ባለሙያዎች መጽሃፉን አንገዛም በሚል በግልጽ አቋማቸውን ቢያሳውቁም ነገር ግን በግዴታ ከደሞዛችሁ የቆረጣል በሚል ወረቀት ፈርሙ መባላቸውን ያነሳሉ።


ሰሞኑን መጽሃፉን በ700 ብር እንዲገዙ መምህራንን ሲያስገድድ የነበረው ስብስብ በቀናት ልዩነት የመጽሃፉን ዋጋ አንድ ሺ ብር አስገብቶታል ሲሉ ለኢትዮ 360 በላኩት መረጃ ላይ አስፍረዋል።


የሪፈራል ሆስፒታሉን ባለሙያዎችና ሰራተኞች ትላንት አስቸኳይ ስብስባ ብሎ የጠራው አካል ያለምንም ቅድመ ሁኔታ መጽሃፉን ትገዛላችሁ፣ይሄም ደግሞ ከደሞዛችሁ ይቆረጣል የሚል አምባገነናዊ ውሳኔ ማሳለፉን ተናግረዋል።


በድሬደዋ የመንግስትና የግል ተቋማት ሰራተኞችን ብር ለመዝረፍ አሰፍስፎ የተነሳው ይሄው አካል በቀጣይ የከተማዋን ነዋሪ ንብረትና ሃብት አልባ ለማድረግ አሰፍስፏል ሲሉም ባለሙያዎቹ በመረጃቸው ላይ አስፍረዋል።


Recent Posts

See All

መስከረም 17/2016 በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ።

በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ። ሰራተኞቹ እየታፈኑ ያሉት ደግሞ በውስጥ በተሰገሰጉ የሰው በላው ስርአት ሃይሎች ጥቆማ ሰጭነት መሆኑን ለኢትዮ 360...

መስከረም 17/2016 በሰሜን ሸዋ ሚዳ መርሃቤቴ ላይ ገድይ ያደረገ ህዝባዊ ሃይሉ በዞኑ የተለያዩ አካባቢዎችን ከሰው በላይ ሃይል ነጻማውጣታቸውን ገለጹ

መርጦ ለማርያምን ነጻ ያወጣው ህዝባዊ ሃይል መቅደላ አምባ አምባ ዩኒቨርስቲ ውስጥና በአካባቢው በሚገኝ ካምፕ ውስጥ መሽጎ የነበረውን ይሄንን ሃይል ማጽዳት ተችሏል ብለዋል። አሁን ላይ ከሁሉም አካባቢ የተባረረው ገዳይ...

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ብርጌድ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ። በጎንደር ዙሪያ ማክሰኝት ወረዳ የጭንጫዬ አርሶ...

Email: ethio360dgre@gmail.com

Phone: 540-277-3242

PayPal ButtonPayPal Button

© 2023 by Ethio360 Media

Connect with Us

  • rumble
  • Telegram
  • TikTok

Support Us

Advertise With Us

bottom of page