top of page

ግንቦት 17/2015በኦሮሚያ ክልል ምናሬ ከተማ ከ150 በላይ የመከላከያ አባላት መገደላቸው ተገለጽ!



በኦሮሚያ ክልል ሙገር ሲሚንቶ ፋብሪካ አካባቢ ምናሬ ከተማ በሚገኘው የመከላከያ ሃይል ላይ የኦነግ ገዳይ ቡድን በፈጸመው ጥቃት ከ150 በላይ የመከላከያ አባላት መገደላቸው የኢትዮ 360 ምንጮች ገለጹ።



ይሄ ቡድን ጥቃቱን የፈጸመው ድንገተኛ ከበባ በማድረግ መሆኑንም ምንጮቹ ሳይጠቁሙ አላለፉም።



ይሄ ቡድን ከፍተኛ ቁጥር ያለውን የመከላከያ ሃይል ከገደለ በኋላ ዲሽቃ መትረየስን ጨምሮ ከባድ መሳሪያዎችን መዝረፉንም ይናገራሉ።


ድንገት ከቦ የጨረሰውን የመከላከያ ሃይል የለበሰውን ወታደራዊ ልብስ ገፎ መውሰዱንም ሳይጠቁሙ አላለፉም።



ይሄ ግድያ ከተፈጸመ በኋላም የኦነጉ ገዳይ ቡድን የመከላከያ ሃይሉ አባላቱ አስከሬን እንዳይነሳ ማድረጉንም ሳይጠቁሙ አላለፉም።



አስቀድሞ ወደ አዲስ አበባ እየመጣሁ ነው ሲል ሲዝት የቆየው ይሄ ገዳይ ቡድን አሁንም ጉዞውን ወደ አዲስ አበባ እያደርገ መሆኑንም በግልጽ መናገር ጀምሯል ብለዋል።



በተለያየ አቅጣጫ ከአዲስ አበባ በ35 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ሃይሉን እያደራጀ ያለው ይሄ ገዳይ ቡድን እንዲህ አይነቱን ጥቃት በመከላከያ ሃይል ላይ ሲፈጽም መረጃው ሙሉ በሙሉ የሚደርሰው ከላይ ካለው የመከላከያ አዛዦች መሆኑንም ያነሳሉ።


በየአካባቢው በዚህ መልኩ እንዲያልቅ እየተደረገ ያለው የመከላከያ ሃይል በዋናነት ጥቃት የሚፈጸምበትም በራሱ አዛዦች መረጃ ሰጭነትና መንገድ መሪነት መሆኑን ኢትዮ 360 በተደጋጋሚ በመረጃው ሲያወጣ መቆየቱ ይታወሳል።


Recent Posts

See All

መስከረም 17/2016 በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ።

በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ። ሰራተኞቹ እየታፈኑ ያሉት ደግሞ በውስጥ በተሰገሰጉ የሰው በላው ስርአት ሃይሎች ጥቆማ ሰጭነት መሆኑን ለኢትዮ 360...

መስከረም 17/2016 በሰሜን ሸዋ ሚዳ መርሃቤቴ ላይ ገድይ ያደረገ ህዝባዊ ሃይሉ በዞኑ የተለያዩ አካባቢዎችን ከሰው በላይ ሃይል ነጻማውጣታቸውን ገለጹ

መርጦ ለማርያምን ነጻ ያወጣው ህዝባዊ ሃይል መቅደላ አምባ አምባ ዩኒቨርስቲ ውስጥና በአካባቢው በሚገኝ ካምፕ ውስጥ መሽጎ የነበረውን ይሄንን ሃይል ማጽዳት ተችሏል ብለዋል። አሁን ላይ ከሁሉም አካባቢ የተባረረው ገዳይ...

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ብርጌድ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ። በጎንደር ዙሪያ ማክሰኝት ወረዳ የጭንጫዬ አርሶ...

Email: ethio360dgre@gmail.com

Phone: 540-277-3242

PayPal ButtonPayPal Button

© 2023 by Ethio360 Media

Connect with Us

  • rumble
  • Telegram
  • TikTok

Support Us

Advertise With Us

bottom of page