top of page

ግንቦት 22/2015በደብረብርሃን ጠባሴ ክፍለ ከተማ ተከራይተው ከሚኖሩበት ቤት በድንገት ውጡ መባሉ ተገለጽ!


በደብረብርሃን ጠባሴ ክፍለ ከተማ ተከራይተው ከሚኖሩበት ቤት በድንገት ውጡ የተባሉት የከተማዋ ነዋሪዎች መሄጃ አተው ችግር ላይ ወድቀዋል ሲሉ ነዋሪዎቹ ለኢትዮ 360 ገለጹ።



በክፍለ ከተማው በንጉስ ሳህለ ስላሴ ቀበሌ ነዋሪው የሆኑት ተከራዮች አቀድሞ በአስር ቀን እንዲወጡ ከታዘዙ በኋላ እሱ ተቀይሮ ዛሬውኑ ልቀቁ መባላቸው መሄጂያ እንዲያጡ አድርጓቸዋል ይላሉ።



በድንገት ከቤታችሁ ውጡ የተባሉት እነዚህ ነዋሪዎች የኪራይ ቤት እንዳያገኙ እንኳን በተፈናቃይ በተሞላው የደብረብርሃን ከተማ ውስጥ የኪራይ ቤት ማግኘት ከባድ ሆኑላ ሲሉ ሁኔታውን ያስቀምጣሉ።




እነዚህ ነዋሪዎች ቤቱን በድንገት እንዲለቁ የተደረጉት ደግሞ ራሱ ነዋሪውን ለመግደል ወደ አካባቢው ለሚገባው የኦህዴዱ ሃይል ነው ይላሉ።



ነዋሪውን በዚህ መልኩ እያጣደፈ ሜዳ ላይ እንዲወድቁ ያደረገው የቤቱ ባላቤት ባለሃብት ቤቱን መሳሪያውን ጠምዶ ህዝብን ለመጨረስ እቅድ ላለው አካል ለማስረከብ ነው ሲሉም በሃዘኔታ ገልጸዋል።


የከተማዋ ነዋሪ የሆነውና ቀማው የተባለው ይሄው ባለሃብት ከማንም እውቅና ውጪ ይሄንን ሃይል ወደ እሱ ቤት ለማስገባት ዞን ላይ የጨረሰው ጉዳይ ሳይሆን አይቀርም ሲሉም ግምታቸውን ያስቀምጣሉ።


Recent Posts

See All

መስከረም 17/2016 በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ።

በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ። ሰራተኞቹ እየታፈኑ ያሉት ደግሞ በውስጥ በተሰገሰጉ የሰው በላው ስርአት ሃይሎች ጥቆማ ሰጭነት መሆኑን ለኢትዮ 360...

መስከረም 17/2016 በሰሜን ሸዋ ሚዳ መርሃቤቴ ላይ ገድይ ያደረገ ህዝባዊ ሃይሉ በዞኑ የተለያዩ አካባቢዎችን ከሰው በላይ ሃይል ነጻማውጣታቸውን ገለጹ

መርጦ ለማርያምን ነጻ ያወጣው ህዝባዊ ሃይል መቅደላ አምባ አምባ ዩኒቨርስቲ ውስጥና በአካባቢው በሚገኝ ካምፕ ውስጥ መሽጎ የነበረውን ይሄንን ሃይል ማጽዳት ተችሏል ብለዋል። አሁን ላይ ከሁሉም አካባቢ የተባረረው ገዳይ...

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ብርጌድ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ። በጎንደር ዙሪያ ማክሰኝት ወረዳ የጭንጫዬ አርሶ...

Email: ethio360dgre@gmail.com

Phone: 540-277-3242

Donate with PayPal

© 2023 by Ethio360 Media

Connect with Us

  • rumble
  • Telegram
  • TikTok

Support Us

Advertise With Us

bottom of page