top of page

ግንቦት 22/2015በፌደራል መስሪያ ቤቶች የሚመጡ የትምህርት እድሎች ለአማራ ተወላጆች እንዳይሰጡ መመሪያ መውረዱን የኢትዮ 360 ምንጮች አስታወቁ።


በፌደራል ፓሊስ ዉስጥ የበዛና ግራ የሚያጋባ ስራ እየተሰራ ነዉ የሚሉት ምንጮቹ አንዳንድ የዉጭ ሀገር የትምህርት እድል ሲመጣ በግልፅ አማራ እዳይከተት የሚል መመሪያ ከእያንዳንዱ አመራር መሰማቱን ቀጥሏል ይላሉ።


የትምህርት እድሉ በብዛት ለባለጊዜዎቹ የሚሰጥ ሲሆን ለደቡብ ተወላጆች የሚሰጥ እድል ካለ ደግሞ የጉራጌ ተወላጆችን እንዳያካትት የሚለውም በመመሪያ ደረጃ የወረደ ነው ብለዋልምንጮች።


የአማራ ተወላጆችም ሆኑ የጉራጌ ተወላጆች በውጭ ሃገር የትምሀር እድል እንዳይሳተፉ ማድረግ ብቻ ሳይሆን ማንኛውም ጥቅማ ጥቅም ያስገኛሉ በሚባሉ ጉዳዮች ውስጥም የአማራና ተጉራጌ ተወላጆች አይካተቱም ብለዋል።


ምናልባትም አሁን ላይ ያለው ሰው በላው ስርአት እየሄደበት ያለው ርቀት አንድና ሁለት ብሔርን ብቻ ሳይሆን ሁሉንም ኢትዮጵያ ወደ ህዝባዊ እምቢተኝነት እንዲሄድ የሚያደርግ ነው ሲሉ አዝማሚያውን ያስቀምጣሉ።


በተለይ ደግሞ በፌደራል ፖሊስ፣በመከላከያ፣በደህንነትና በአጠቃላይ በጸጥታው ዘርፍ ላይ የተሰማሩ ባለሙያዎች ላይ የሚደረገው ጫና ነገሮችን ወደ ሌላ አቅጣጫ እየፉአቸውን ነው ሲሉ የኢትዮ 360 ምንጮች ገልጸዋል።


Recent Posts

See All

መስከረም 17/2016 በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ።

በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ። ሰራተኞቹ እየታፈኑ ያሉት ደግሞ በውስጥ በተሰገሰጉ የሰው በላው ስርአት ሃይሎች ጥቆማ ሰጭነት መሆኑን ለኢትዮ 360...

መስከረም 17/2016 በሰሜን ሸዋ ሚዳ መርሃቤቴ ላይ ገድይ ያደረገ ህዝባዊ ሃይሉ በዞኑ የተለያዩ አካባቢዎችን ከሰው በላይ ሃይል ነጻማውጣታቸውን ገለጹ

መርጦ ለማርያምን ነጻ ያወጣው ህዝባዊ ሃይል መቅደላ አምባ አምባ ዩኒቨርስቲ ውስጥና በአካባቢው በሚገኝ ካምፕ ውስጥ መሽጎ የነበረውን ይሄንን ሃይል ማጽዳት ተችሏል ብለዋል። አሁን ላይ ከሁሉም አካባቢ የተባረረው ገዳይ...

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ብርጌድ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ። በጎንደር ዙሪያ ማክሰኝት ወረዳ የጭንጫዬ አርሶ...

Email: ethio360dgre@gmail.com

Phone: 540-277-3242

PayPal ButtonPayPal Button

© 2023 by Ethio360 Media

Connect with Us

  • rumble
  • Telegram
  • TikTok

Support Us

Advertise With Us

bottom of page