top of page

ግንቦት 23/2015 በሐዋሳ ከተማ ከንቲባ የግል ጠባቂ የታፈነችው ወይዘሪት ጸጋ በላቸው እስካሁን ያለችበት ሊታወቅ አለመቻሉን የኢትዮ 360 ምንጮች ገለጹ።


በሐዋሳ ከተማ ከንቲባ የግል ጠባቂ የታፈነችው ወይዘሪት ጸጋ በላቸው እስካሁን ያለችበት ሊታወቅ አለመቻሉን የኢትዮ 360 ምንጮች ገለጹ።


የዳሽን ባንክ የሂሳብ ሠራተኛ የሆነችው ወይዘሪት ጸጋ በላቸው በከንቲባው ጠባቂ የታገተችው ግንቦት 15/2015 ከሥራ ወደ ቤት እየተመለሰች ባለችበት ወቅት እንደነበር ያነሳሉ።


ታፋኟ የወልቂጤ ከተማ ተወላጅ ስትሆን ወደ ሀዋሳ ከተማ የመጣችውም ባለፈው ዓመት ዳሽን ባንክ ተቀጥራ ለሥራ እንደሆነም አስታውሰዋል።


የተጠላፊዋ ቤተሰቦች ጉዳዩን ለሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት በማሳወቅ ክትትል ላይ ቢሆኑም እስካሁን ግን የተጠላፊዋ ደብዛ ሊገኝ አልቻለም ባይ ናቸው።


ይህ አፈና ከተፈጸመ ሳምንት የሞላው ቢሆንም ጉዳዩ ወደ ህዝብ ጆሮ እንዳይደርስ ተደርጎ እንደቆየም ሳይጠቁሙ አላልፉም።


ይህ በእንዲህ እንዳለም በየአካባቢው በኦህዴዱ ሃይል የሚደረገው አፈና አሁንም ተጠናክሮ መቀጠሉን ሳይጠቁሙ አላለፉም።


በብዙ ስራዎቹ የሚታወቀው አርቲስት ተሾመ አየለ በዚህ ሃይል ትላንት ሲታፈን የፍኖተ ህይወት በጎ አድራጎት ማህበር ሰብሳቢ ወጣት ንጉሴ ዋለልኝም በዚሁ ስብስብ ወደ አልታወቀ ስፍራ ታፍኖ መወሰዱን አመልክተዋል።


ታፍነው በየቦታው እየተጋዙ ያሉ ንጹሃን ዜጎችም በየማጎሬያው ያለምንም ምግብና ውሃ እንዲሰቃዩ እየተደረጉ መሆኑንም ነው ምንጮቹ ያመለከቱት።


ምናልባትም በአንድ ቦታ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ሰዎች እንዲታጎሩ ከመደረጉ ጋርም ተያይዞ ምናልባትም ንጹሃን ዜጎቹ ለተለያዩ በሽታዎች ሊጋለጡ ይችላሉ ሲሉም ምንጮቹ ስጋታቸውን አስቀምጠዋል።


Recent Posts

See All

መስከረም 17/2016 በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ።

በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ። ሰራተኞቹ እየታፈኑ ያሉት ደግሞ በውስጥ በተሰገሰጉ የሰው በላው ስርአት ሃይሎች ጥቆማ ሰጭነት መሆኑን ለኢትዮ 360...

መስከረም 17/2016 በሰሜን ሸዋ ሚዳ መርሃቤቴ ላይ ገድይ ያደረገ ህዝባዊ ሃይሉ በዞኑ የተለያዩ አካባቢዎችን ከሰው በላይ ሃይል ነጻማውጣታቸውን ገለጹ

መርጦ ለማርያምን ነጻ ያወጣው ህዝባዊ ሃይል መቅደላ አምባ አምባ ዩኒቨርስቲ ውስጥና በአካባቢው በሚገኝ ካምፕ ውስጥ መሽጎ የነበረውን ይሄንን ሃይል ማጽዳት ተችሏል ብለዋል። አሁን ላይ ከሁሉም አካባቢ የተባረረው ገዳይ...

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ብርጌድ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ። በጎንደር ዙሪያ ማክሰኝት ወረዳ የጭንጫዬ አርሶ...

bottom of page