top of page

ግንቦት 29/2015በአዲስ አበባ የሚገኘው የባህል አልባሳት መደብር ሙሉ በሙሉ መዘጋቱን ነዋሪዎቹ ገለጹ



በአዲስ አበባ በተለምዶ ሽሮ ሜዳ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የሚገኘው የባህል አልባሳት መደብር ሙሉ በሙሉ መዘጋቱን ነዋሪዎቹ ለኢትዮ 360 ገለጹ።



ለንግድ መደበሩ መታሸግ ዋናው ምክንያት ደግሞ አስቀድሞ መደብሮቹ ለታሪክ በማይቆረቆሩ ካድሬዎች እንዲሞላ በመደረጉ ነው ይላሉ።



የባለጊዜው የቀኝ እጅ መሆናቸው ደግሞ የአካባቢው ማህበረሰብ በተደጋጋሚ ይሄ እንዳይደርስና የሚፈጸመው ወንጀል ይቁም ሲል እነሱ ደግሞ ስርአቱን በመደገፍ ላይ ነበሩ ብለዋል ለኢትዮ360።



አሁንም ድምጽ ማሰማት የተጀመረው በራሳቸው ስለመጣ እንዲ በሌላ አይደለም ባይ ናቸው የሚል መሆኑን ያነሳሉ።


ነባሩን ኮንቴነሩን አፍርሶ ከአካባቢው ያባረረው አካል ቦታውን ያስረከበው ለካድሬዎች ስብስብ መሆኑን ያነሳሉ።


አሁንም እነዚህ የባህል አልባሳት መደብሮች እንዲፈርሱ እንዳይነሱ ተደርገው የተዘጉት እስር በርሳቻው ስላልተሳማሙ እንጂ ሌላ አይደለም ባይ ናቸው።



ሙሉ በሙሉ መደብሮቹን ያሸገው አካል አካባቢውን በገመድ ከልሎ በወታደር እያስጠበቀው ነው ብለዋል።

መደብሮቹን ተረክበው የነበሩት ሰዎች አሁን ላይ ጥቅማቸው ሲነካ ድምጽ ያሰሙ እንጂ ከእንጦጦ አምባ ትምህርት ቤት ችግር ጋር ተያይዞ ተማሪ ጠቋሚና አሳሳሪ በመሆን ሲሳተፉ እንደነበርም ያነሳሉ።



የአካባቢው ማህበረሰብ ይሄ ታሪካዊ ቅርስ እንዳይጠፋና አካባቢውም በዚህ ደረጃ እንዳይወድም ሲታገሉ መቆየታቸውንም ነው ለኢትዮ 360 የገለጹት።


Recent Posts

See All

መስከረም 17/2016 በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ።

በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ። ሰራተኞቹ እየታፈኑ ያሉት ደግሞ በውስጥ በተሰገሰጉ የሰው በላው ስርአት ሃይሎች ጥቆማ ሰጭነት መሆኑን ለኢትዮ 360...

መስከረም 17/2016 በሰሜን ሸዋ ሚዳ መርሃቤቴ ላይ ገድይ ያደረገ ህዝባዊ ሃይሉ በዞኑ የተለያዩ አካባቢዎችን ከሰው በላይ ሃይል ነጻማውጣታቸውን ገለጹ

መርጦ ለማርያምን ነጻ ያወጣው ህዝባዊ ሃይል መቅደላ አምባ አምባ ዩኒቨርስቲ ውስጥና በአካባቢው በሚገኝ ካምፕ ውስጥ መሽጎ የነበረውን ይሄንን ሃይል ማጽዳት ተችሏል ብለዋል። አሁን ላይ ከሁሉም አካባቢ የተባረረው ገዳይ...

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ብርጌድ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ። በጎንደር ዙሪያ ማክሰኝት ወረዳ የጭንጫዬ አርሶ...

Email: ethio360dgre@gmail.com

Phone: 540-277-3242

PayPal ButtonPayPal Button

© 2023 by Ethio360 Media

Connect with Us

  • rumble
  • Telegram
  • TikTok

Support Us

Advertise With Us

bottom of page