top of page

ግንቦት 29/2015በአፋር ክልል በሾላ ወታደራዊ ካምፕ ውስጥ ታጉረው የሚገኙትና የአማራ ተወላጅ ሕይወታቸው በከባድ አደጋ ላይ መውደቁን ተገለጹ።



በአፋር ክልል በሾላ ወታደራዊ ካምፕ ውስጥ ታጉረው የሚገኙትና ቁጥራቸው ከ800 በላይ የሚሆን የአማራ ተወላጅ የመከላከያ አባል የነበሩና የፋኖ ህዝባዊ አባላት ሕይወታቸው በከባድ አደጋ ላይ መውደቁን ለኢት 360 ገለጹ።



በወታደራዊ ካምፑ ከታገቱ አንድ አመት እንደሆናቸው የሚናገሩት አባላቱ በካምፑ ውስጥ ምግብ፣ውሃና አልባሳትን ተከልክለው በመከራ ውስጥ መሆናቸውን ይናገራሉ።


በቀን አንዳንድ ኮቾሮ እየተሰጣቸው አንድ ቦታ የታጎሩት የአማራ ተወላጆች ለእለት ማረፊያ በማጣታቸው በቅጠልና በእንጨት ለመስራት መገደዳቸውን ይናገራሉ።



ከሁሉም እየከፋ የመጣው ደግሞ በየጊዜው የሚታመሙ ሰዎች መብዛትና ምንም አይነት የህክምና አገልግሎት አለመኖሩ ነው ይላሉ።



በተለይ ደግሞ በአካባቢው ያለው ሙቀት የበለጠ መከራቸውን እንዳከፋባቸው ተናግረዋል።


የታጎሩበትን ካምፕ እየጠበቀ ላለው ሃይል ጥያቄ ለማቅረብ ቢሞክሩም ምልሽ ግን ማግኘት እንዳልቻሉ ነው ለኢትዮ 360 የገለጹት።


Recent Posts

See All

መስከረም 17/2016 በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ።

በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ። ሰራተኞቹ እየታፈኑ ያሉት ደግሞ በውስጥ በተሰገሰጉ የሰው በላው ስርአት ሃይሎች ጥቆማ ሰጭነት መሆኑን ለኢትዮ 360...

መስከረም 17/2016 በሰሜን ሸዋ ሚዳ መርሃቤቴ ላይ ገድይ ያደረገ ህዝባዊ ሃይሉ በዞኑ የተለያዩ አካባቢዎችን ከሰው በላይ ሃይል ነጻማውጣታቸውን ገለጹ

መርጦ ለማርያምን ነጻ ያወጣው ህዝባዊ ሃይል መቅደላ አምባ አምባ ዩኒቨርስቲ ውስጥና በአካባቢው በሚገኝ ካምፕ ውስጥ መሽጎ የነበረውን ይሄንን ሃይል ማጽዳት ተችሏል ብለዋል። አሁን ላይ ከሁሉም አካባቢ የተባረረው ገዳይ...

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ብርጌድ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ። በጎንደር ዙሪያ ማክሰኝት ወረዳ የጭንጫዬ አርሶ...

Email: ethio360dgre@gmail.com

Phone: 540-277-3242

PayPal ButtonPayPal Button

© 2023 by Ethio360 Media

Connect with Us

  • rumble
  • Telegram
  • TikTok

Support Us

Advertise With Us

bottom of page