top of page

መስከረም 3/2015በአዲስ አበባ ዙሪያ በተለያዩ ማጎሪያ ስፍራዎች ከሚገኙ ንጹሃን ዜጎች 150 ያህሉ በወረርሽኝ ህይወታቸው ማለፉን ምንጮች ገለጹ።



በአዲስ አበባ ዙሪያ በተለያዩ ማጎሪያ ስፍራዎች ከሚገኙ ንጹሃን ዜጎች 150 ያህሉ በወረርሽኝ ህይወታቸው ማለፉን የኢትዮ 360 ምንጮች ገለጹ።


በተለይ የነዚህ ንጹሃን ዜጎች ህይወት ያለፈው በገላን፡በቡራዩ፣በሰበታ በሚገኙ ማጎሪያ ስፍራዎች ከሚገኙት ታራሚዎች መካከል መሆኑንም ነው ምንጮቹ ያመለከቱት።


ህይወታቸው ካለፈው አብዛኞቹ ደግሞ የአማራ ተወላጆች መሆናቸውንም ሳይጠቁሙ አላለፉም።


እነዚህ በግፍ ህይወታቸው ያለፈው ንጹሃን ዜጎች አስከሬንም በኦህዴዱ የመከላከያ ተሽከርካሪ ሌሊቱን ሲያጓጉዙ ማደሩን ተናግረዋል።


በስተመጨረሻም አነጋጉ ላይ በብላቴ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ጀርባ በሚገኘው ጫቃ አስከሬናቸው እንዲቀበር መደረጉንም አጋልጠዋል።


ኦቪድ ኮንስትራክሽንን የሚመሩት የገዳዩ ቡድን ተባባሪዎች አሁንም በየቦታው የማጎሪያ ስፍራዎችን በመገንባት ንጹሃንን እያስጨረሱ ነው ሲሉም ምንጮቹ አስታውቀዋል።


ይህ በእንዲህ እንዳለ በመራዊ ከተማ መንገድ ላይ እና ካፌ ውስጥ ተገኝተው የታፈኑ 17 ወጣቶችን በተለምዶ ቻይና ካምፕ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ከወሰዷቸው በኋላ ገደል በማስቆፈር እዛው ገደል ላይ እንዲረሸኑ መደረጉን የኢትዮ 360 ምንጮች ገልጸዋል።


ይሄንን አይነቱ አስነዋሪ ድርጊት እየተፈጸመ ያለው ደግሞ የገዳዩ ቡድንና አድማ ብተና በሚል በአካባቢው የተሰማራው ሃይል መሆኑን ሳይጠቁሙ አላለፉም።


ከዚህም ሌላ በጎጃም አዊ ዞን አዲስ ቅዳም ከተማ አንድ አባት በዚሁ የአድማ ብተና ልብስ ለብሶ ወደ አካባቢው በገባ ቡድን በስለት መዋጋታቸውንም ተናገረዋል።


በወቅቱ ይላሉ ምንጮቹ በ3 ፓትሮል ዲሽቃ የታጠቁ የአድማ ብተና ልብስ የለበሱ ሃይሎች እያለፉ በነበሩበት ሰአት በቁጭት የልጃቸውን ስም በመጥራት ሲያዝኑ የነበሩ አባትን መመልከቱን ገልጸዋል።


ይሄው ስብስብ ከፓትሮል ወርዶ በቀጥታ ወድ አዛውንቱ ከመጣ በኋል በስለት ወግቷቸው መሄዱን ምንጮቹ ተናግረዋል።


ይሄ ስብስብ ይሄንን አሳዛኝ ድርጊት የፈጸመው ደግሞ ህዝብ በተሰበሰበበት መሆኑንም ሳይጠቁሙ አላለፉም።

በጩቤ የተወጉት አዛውንት የፋኖ አስር አለቃ ኤፍሬም አጥናፉ አባት መሆናቸውንም ምንጮቹ ተናግረዋል።


ፋኖ አስር አለቃ ኤፍሬም የፋኖ መስራችና በተለያዩ ቦታወች በሽዎች የሚቆጠሩ ፋኖዎችን ያሰለጠነ ፣በህዋት ጦርነት የጋሸናን ምሽግ ሰብሮ የተሰዋ ጀግና ልጃቸውን ስም ስለጠሩ ብቻ በስለት ተወግተዋል ሲሉ ምንጮቹ በሃዘን ተናግረዋል።


አባትዬው በጩቤ ከተወጉ በኋላ አሁን ያሉበትን ሁኔታ ማወቅ እንዳልተቻለም ምንጮቹ አመልክተዋል።




Recent Posts

See All

መስከረም 17/2016 በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ።

በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ። ሰራተኞቹ እየታፈኑ ያሉት ደግሞ በውስጥ በተሰገሰጉ የሰው በላው ስርአት ሃይሎች ጥቆማ ሰጭነት መሆኑን ለኢትዮ 360...

መስከረም 17/2016 በሰሜን ሸዋ ሚዳ መርሃቤቴ ላይ ገድይ ያደረገ ህዝባዊ ሃይሉ በዞኑ የተለያዩ አካባቢዎችን ከሰው በላይ ሃይል ነጻማውጣታቸውን ገለጹ

መርጦ ለማርያምን ነጻ ያወጣው ህዝባዊ ሃይል መቅደላ አምባ አምባ ዩኒቨርስቲ ውስጥና በአካባቢው በሚገኝ ካምፕ ውስጥ መሽጎ የነበረውን ይሄንን ሃይል ማጽዳት ተችሏል ብለዋል። አሁን ላይ ከሁሉም አካባቢ የተባረረው ገዳይ...

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ብርጌድ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ። በጎንደር ዙሪያ ማክሰኝት ወረዳ የጭንጫዬ አርሶ...

Email: ethio360dgre@gmail.com

Phone: 540-277-3242

PayPal ButtonPayPal Button

© 2023 by Ethio360 Media

Connect with Us

  • rumble
  • Telegram
  • TikTok

Support Us

Advertise With Us

bottom of page