top of page

መስከረም 8/2016በኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ውጪ ለመውጣት የሚሞክሩ ሰዎች አላግባብ የሆነ ገንዘብ እየተጠየቁ መሆኑን መንገደኞቹ ገለጹ።



በኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ውጪ ለመውጣት የሚሞክሩ ሰዎች አላግባብ የሆነ ገንዘብ እየተጠየቁ መሆኑን መንገደኞቹ ለኢትዮ 360 ገለጹ።


መንገደኞቹ ወደ ተለያዩ ሃገራት ያደርጓቸው የነበሩት ጉዞዎች አላግባብ ክፍያ በመጠየቃቸው ብቻ ጉዟቸው ለቀናት መጓተቱን ለኢትዮ 360 በላኩት መረጃ ላይ አስፍረዋል።


እያንዳንዱ መንገደኛ ለሚያደርገው ጉዞ ከኢሚግሬሽን ሰራተኞች በትንሹ ከ10ሺ እስከ 30ሺ ብር ገንዘብ እንደሚጠየቁም ተናግረዋል።


ይሄ ገንዘብ ሲጠየቅ ደግሞ መንገደኛው ተጨማሪ አገልግሎት እፈልጋለሁ ብሎ ሳይሆን መሄድ ከፈለክ ይሄን ያህል ገንዘብ መክፈል አለብህ የሚል ህገወጥና አይን ያወጣ የሌብነት ጥያቄ ከነዚሁ የስርአቱ ሰራተኞች ስለሚቀርበለት ነው ይላሉ።


ትኬት ወደ ቆረጡበት ሃገር እንዳይሄዱ የተከለከሉና ገንዘብ አምጡ የሚባሉት መንገደኞች የሚጠየቁት ብር እንዲቀነስላቸው የኢሚግሬሽኑን የሌቦች ስብስብ የሚያሸማግል ሰውም በመሃል መኖሩን ሳይጠቁሙ አላለፉም።


በአጠቃላይ አሁን ላይ በአየር መንገዱ ውስጥ ያለው አይን ያወጣ ሌብነትና ህገወጥ አሰራር የሃገር ውስጥ መንገደኛውን ብቻ ሳይሆን የውጭ ሃገር ዜጎችንም ጭምር ዋጋ እያስከፈለ ነው ሲሉ በአየር መንገዱ ላይ የተደቀነውን አደጋ አመልክተዋል።

Recent Posts

See All

መስከረም 17/2016 በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ።

በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ። ሰራተኞቹ እየታፈኑ ያሉት ደግሞ በውስጥ በተሰገሰጉ የሰው በላው ስርአት ሃይሎች ጥቆማ ሰጭነት መሆኑን ለኢትዮ 360...

መስከረም 17/2016 በሰሜን ሸዋ ሚዳ መርሃቤቴ ላይ ገድይ ያደረገ ህዝባዊ ሃይሉ በዞኑ የተለያዩ አካባቢዎችን ከሰው በላይ ሃይል ነጻማውጣታቸውን ገለጹ

መርጦ ለማርያምን ነጻ ያወጣው ህዝባዊ ሃይል መቅደላ አምባ አምባ ዩኒቨርስቲ ውስጥና በአካባቢው በሚገኝ ካምፕ ውስጥ መሽጎ የነበረውን ይሄንን ሃይል ማጽዳት ተችሏል ብለዋል። አሁን ላይ ከሁሉም አካባቢ የተባረረው ገዳይ...

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ብርጌድ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ። በጎንደር ዙሪያ ማክሰኝት ወረዳ የጭንጫዬ አርሶ...

Email: ethio360dgre@gmail.com

Phone: 540-277-3242

PayPal ButtonPayPal Button

© 2023 by Ethio360 Media

Connect with Us

  • rumble
  • Telegram
  • TikTok

Support Us

Advertise With Us

bottom of page