top of page

ጳጉሜ 2/2015 አዲስ ተመሰረተ የተባለው ክልል የመንግስት ሰራተኛውን ከግምት ባስገባ መልኩ አለመደራጀቱ ሰራተኞቹ ገለጹ።



የደቡብ ክልል በሚል አዲስ ተመሰረተ የተባለው ክልል የመንግስት ሰራተኛውን ከግምት ባስገባ መልኩ አለመደራጀቱ ዋጋ እያስከፈላቸው መሆኑን ሰራተኞቹ ለኢትዮ 360 ገለጹ።




ማህበሩ የቀድሞው የደቡብ ክልል በአራት ክልሎች መደራጀትን ተከትሎ በመንግስት ሰራተኛው ላይ እየደረሰ ያለው በደል ላይ ትኩረት ያደረገ ውይይት እያካሄደ ነው ሲሉም ምንጮቹ ተናግረዋል።



ነገር ግን ማህበሩም ሆነ ሰራተኛው መብቱን በተለያየ መንገድ እየጠየቀ ባለበት በዚህ ሰአት ግን የደቡብ ኢትዮጵያም ሆነ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ በሚል የተመሰረቱት ክልሎች አመራሮች ግን የሰራተኛውን ጉዳይ ለአፍታም ማሰብ አይፈልጉም ሲሉ ያለውን እወነታ አስቀምጠዋል።



ይልቁንም የሰራተኛውን ችግር ከመፍታት ይልቅ ለሹመት መሽቀዳደም እና ስራ ጀምረናል በሚል ማህበራዊ ሚዲያውን ማጨናነቅን የዘወትር ስራቸው አድርገውታል ብለዋል ሰራተኞቹ በመረጃቸው።


የክልል አደረጃጀትን በበላይነት ለመምራት በህግ ስልጣን የተሰጠው ፕሮጀክት ጽህፈትቤት የሰራተኛውን ጉዳይ ጆሮ ዳባ ልበስ ያለ ይመስላል።


በፕሮጀክት ጽህፈት ቤት ተሰራ የተባለው የሰራተኞች የስራ ድልድልም ቢሆን ከመስፈርቱና ከህጉ ጋር የተጣረሰ ነው ሲሉ ሰራተኞቹ በመረጃቸው ተናግረዋል።


ከዚህም ጋር ተያይዞ ቁጥራቸው ከፍተኛ የሆኑ ሰራተኞች ወደ ተቃውሞ መግባታቸውን አመልክተዋል።


ሰራተኞቹ ከተቃውሞም ሌላ በድልድል መስጫ መስፈርቱ ላይ ያቀረቡት ቅሬታ በሁለት ቀናት ምላሽ ያገኛል ቢባልም ቅሬታው ከቀረበ ግን ከ20 ቀን በላይ ሆኖታል ብለዋል።


የሰራተኛውን መብት ይዞ ከክልል እስከ ፌደራል የሰራተኛውን መብት ለማስከበር እየለፋ ያለው የሰራተኛ ማህበሩ ከሁሉም አካል ምላሽ የማያገኝ ከሆነ ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት ለመውሰድ እንደሚገደድም ነው ሰራተኞቹ ለኢትዮ 360 በላኩት መረጃ ላይ ያሰፈሩት።


Recent Posts

See All

መስከረም 17/2016 በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ።

በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ። ሰራተኞቹ እየታፈኑ ያሉት ደግሞ በውስጥ በተሰገሰጉ የሰው በላው ስርአት ሃይሎች ጥቆማ ሰጭነት መሆኑን ለኢትዮ 360...

መስከረም 17/2016 በሰሜን ሸዋ ሚዳ መርሃቤቴ ላይ ገድይ ያደረገ ህዝባዊ ሃይሉ በዞኑ የተለያዩ አካባቢዎችን ከሰው በላይ ሃይል ነጻማውጣታቸውን ገለጹ

መርጦ ለማርያምን ነጻ ያወጣው ህዝባዊ ሃይል መቅደላ አምባ አምባ ዩኒቨርስቲ ውስጥና በአካባቢው በሚገኝ ካምፕ ውስጥ መሽጎ የነበረውን ይሄንን ሃይል ማጽዳት ተችሏል ብለዋል። አሁን ላይ ከሁሉም አካባቢ የተባረረው ገዳይ...

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ብርጌድ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ። በጎንደር ዙሪያ ማክሰኝት ወረዳ የጭንጫዬ አርሶ...

Email: ethio360dgre@gmail.com

Phone: 540-277-3242

Donate with PayPal

© 2023 by Ethio360 Media

Connect with Us

  • rumble
  • Telegram
  • TikTok

Support Us

Advertise With Us

bottom of page