top of page

ሐምሌ 13/2015 በቤንሻንጉል በኦህዴዱ ኦነግ በእርቅ ስም ገብቶ የነበረው የጉምዝ ታጣቂ ቡድን ተመልሶ ጭካ መግባቱን ነዋሪዎቹ ገለጹ።


በቤንሻንጉል በኦህዴዱ ኦነግ በእርቅ ስም ገብቶ የነበረው የጉምዝ ታጣቂ ቡድን ተመልሶ ጭካ መግባቱን ነዋሪዎቹ ለኢትዮ 360 ገለጹ።


ግልገል ሲቀለብና በገዳዩ ስርአት ሲሰለጥን የቆየው ይሄው ገዳይ ቡድን ጫካ መግባቱን ተከትሎ በግልገልም ሆነ በማንዱራ ከባድ ስጋት ሰፍኗል ብለዋል።


ይሄንን ገዳይ ቡድን የኦህዴዱ መከላከያ ሃይል ከቦታል የሚል ፕሮፓጋንዳ ለማህበረሰቡ እንዲነዛ ከተደረገ በኋላ ለሊቱን ከአካባቢው እንዲወጣ ተደርጓል ብለዋል።


ቁጥራቸውን ለማጣራት ባይችሉም ብዛት እንዳላቸው ግን ማወቅ መቻላቸውን ይናገራሉ።


ዋናው ተደራጅቶ ሰልጥኖ እንዲላክ የተደረገው ለሌላ ሳይሆን ንጹሃንን እንዲገል ለማድረግ ነው ሲሉ ለኢትዮ 360 ገልጸዋል።



እንኳን ይሄ አራጅ ቡድን ተጨምሮ ተለቆ አይደለም አስቀድሞም ቢሆን ከቤት ወቶ በሰላም ለመመለስ የነበረው ስጋት አሁንም እንደቀጠለ መሆኑንም ሳይገልጹ አላለፉም።

 
 

Support Us

Donate with PayPal

© 2025 by Ethio360 Media

Connect with Us

  • rumble
  • Telegram
  • TikTok
bottom of page