top of page

(ኢትዮ 360 - ሐምሌ 13/2015) ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ አስፋው ከሃገሩ ተሰደደ።


በተደጋጋሚ በገዳዩ ስርአት ማፈኛ ቤቶች እንዲማቅቅ የተደረገው ጋዜጠኛ ቴድሮስ አስፋው አሁን ባለው ሁኔታ በሃገር ውስጥ የሚያንቀሳቅስ ነገር ባለመኖሩ የሚወዳት ኢትዮጵያንና የሚወደውን ሙያውን ትቶ ለመሰደድ መገደዱን ለኢትዮ 360 ገልጿል።



በተደጋጋሚ በሚያሳቸው ሃሳቦችና የገዳዩ ስርአትን በአደባባይ በማጋለጥ የሚታወቀው ጋዜጠኛው በተደጋጋሚ በታፈነበት ወቅት ያደርሱበት የነበረው የሰብአዊ መብት ጥሰት ከፍተኛ የመብት ጥሰትና እውነትን ለማፈን የደረግ የነበረው ርብርብ እዚህ ውሳኔ ላይ እንዲደርስ እንዳደረገውም ተናግሯል።



ጋዜጠኛ ቴድሮስ አስፋው ከሐገር መውጣቱ ጋር ተያይዞ ለኢትዮ 360 በሰጠው መረጃ እንደ ሃገር ያለው ሁኔታ የማያሰራ ብቻ ሳይሆን ለህይወት አስጊ የሚባል ደረጃ ላይ በመድረሱ ከሃርገ ለመኮብለል መገደዱን ነው የተናገረው።



 
 

Support Us

Donate with PayPal

© 2025 by Ethio360 Media

Connect with Us

  • rumble
  • Telegram
  • TikTok
bottom of page