top of page

ኢትዮ 360 - ሐምሌ 19/2015)በዱባይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ፓስፖርት የሚያድስላቸው አካል ጠፍቶ ለከፋ ችግር ተጋልጠዋል።


በተባበሩት አረብ ኢምሬትስ ዱባይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ፓስፖርት የሚያድስላቸው አካል በማጣታቸው ለከፋ ችግር መጋለጣቸውን ለኢትዮ 360 ገለጹ።


ፓስፖርት ለማሳደስ ኤምባሲውን ሲለምኑ ወደ ሰባት ወራትን ማስቆጠሩን ይናገራሉ።

ከኤምባሲው ጠብቁ የሚሉ ተደጋጋሚ ምላሾች ቢሰጡም እስካሁን ግን በመጠበቅ የተገኘ ነገር የለም ብለዋል።


እስከ ሰኔ 30 ፓስፖርታችሁ ታድሶ ይመጣሉ የሚል ቃል ተገብቶ የነበረ ቢሆንም እስካሁን ግን ምንም ሊያደርጉ አልቻሉም ብለዋል።


ፓስፖርታቸውን ለማሳደስ ለኤምባሲው በሰጡበት እዛው የመገልገያ ጊዜውን እንደተቃጠለም ሳይገልጹ አላለፉም።


ነጭ ወረቀት ሰቶ በእሱ ተጠቀሙ የሚለው ኤምባሲ በራሱ መፍትሄ ለማምጣት አልቻለም ብለዋል።

አምባሳደሩን ጭምር አናግረናል የሚሉት ኢትዮጵያውያኑ ነገር ግን ማንም የመፍትሄው አካል ሊሆን ባለመቻሉ ኢትዮጵያውያኑ በአሰሪዎቻቸው ያለምንም ማስረጃ እየተጫኑ መሆኑን አስታውቀዋል።


በሰው ሃገር ያለፓስፖርት መንቀሳቀስም ሆነ የቤት ኪራይ መክፈልም ሆነ የባንክ አገልግሎት ማግኘት እንደማይቻል እየታወቀ ማንም ግን ሊያግዛቸው እንዳልቻለ ነው ለኢትዮ 360 የገለጹት።


 
 

Support Us

Donate with PayPal

© 2025 by Ethio360 Media

Connect with Us

  • rumble
  • Telegram
  • TikTok
bottom of page