top of page

(ኢትዮ 360-ሰኔ 14/2015)የታገቱትን የህዝብ ማመላለሻ አሽከርካሪዎችን ለማስፈታት ለእያንዳንዱ አንድ ሚሊየን ብር ተጠየቀ።


በኦሮሚያ ክልል አሊ ዴሮ አካባቢ የታገቱትን የህዝብ ማመላለሻ አሽከርካሪዎችን ለማስፈታት ለእያንዳንዱ አንድ ሚሊየን ብር መጠየቃቸውን ቤተሰቦቻቸው ለኢትዮ 360 ገለጹ።


ምንም ማድረግ አልቻልንም የሚሉት ቤተሰቦቻቸው ገንዘቡን ሰተው ወገኖቻቸውን በህይወት ለማስመለስ እየሞከሩ መሆኑን ይናገራሉ።


አሽከርካሪዎቹ ብቻ ቁጥራቸው ወደ 34 ይደርሳል የሚሉት ቤተሰቦቻቸው ከነሱም በተጨማሪ ሌሎች ተሳፋሪዎችን ጨምሮ ከ60 በላይ እንደሚሆኑም ይናገራሉ።


ለዚህ ሁሉ ታጋች ደግሞ እንደ ሰው ታይተው ሳይሆን እንደ ከብት መደብ ዋና ይወጣለታል ሲሉ በሃዘኔታ ይገልጻሉ።


ይሄንን ብር ለመክፈል ደግሞ አማራው ቤቱንም ሆነ ያለውን ከብቱን በመሸጥና ወገኑን ለማዳን እየጣረ ነው ሲሉ ለኢትዮ 360 ገልጸዋል።

 
 

Support Us

Donate with PayPal

© 2025 by Ethio360 Media

Connect with Us

  • rumble
  • Telegram
  • TikTok
bottom of page