top of page

ግንቦት 23/2015 በሰሜን ሸዋ መንዝና አካባቢው በኦህዴዱ የመከላከያ ሃይል መወረሩን ነዋሪዎቹ ለኢትዮ 360 ገለጹ።


በሰሜን ሸዋ መንዝና አካባቢው በኦህዴዱ የመከላከያ ሃይል መወረሩን ነዋሪዎቹ ለኢትዮ 360 ገለጹ።

ወደ አካባቢው የገባው ይሄው ሃይል ደግሞ ሞላሌ አካባቢ ቆሎ ማርገፊያ በሚባል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መመሸጉን ይናገራሉ።

ተማሪዎቹም ሆኑ መምህራኑ ጦር መሳሪያ ከያዘ አካል ጋር ሆኖ እንዴት ትምህርት መማር ይቻላል በሚል እምቢተኝነታቸውን ቢገልጹም የወረዳው አመራር ግን ጫና እያደረገባቸው መሆኑን አመልክተዋል።


ይሄ ሃይል ከባድ መሳሪያን ጨምሮ ሌሎች መሳሪያዎችን ይዞ በዛው ትምህርት ቤት መመሸጉን ነዋሪዎቹ ገልጸዋል።


መንዝ ላይ እስካሁን ጦርነቱን ባይጀምር አስቀድሞ ግን መንዝ ቀያ ላይ ህዝብን ያነቃሉ የሚባሉ ሰዎችን እያፈነ መሆኑንም ነዋሪዎቹ ለኢትዮ 360 ገልጸዋል።



 
 

Support Us

Donate with PayPal

© 2025 by Ethio360 Media

Connect with Us

  • rumble
  • Telegram
  • TikTok
bottom of page